ፀሎተ ንድራ

         ዓውደ ነገሥት

 

                   ወፍካሬ ከዋክብት

 

                     (ሥነ ምርምር)

 

 

   በጥንታውያን የኢትዮጵያ ሊቃውንቶችና ጠበብቶች የተዘጋጀ

                     ብሔራዊ ቅርስ

 

                    ፲፱፻፶፫ ዓ.ም

 

 

      ኃጢአትን የሚያደርግ ሁሉ ሕግንም መተላለፍ ያደርጋል።ኃጢአትም እርሱ ሕግን መተላለፍ ነው።

 

      እናንትም ታውቃላችሁ ክርስቶስ ኢየሱስ እንደተገለጠ ኃጢአታችንን ሊያስወግድ። ኃጢአትም በርሱ የለም። በእርሱ የሚኖር ሁሉ ኃጢአት አይሠራም ኃጢአት የሚሠራ ሁሉ አላየውም አላወቀውምም።

 

      ልጆች ሆይ ማንም አያስታችሁ። ጽድቅ የሚያደርግ ጻድቅ ነው ያም ጻድቅ እንደሆነ። ኃጢአትም የሚያደርግ እርሱ ከሰይጣን ነው። ሰይጣን ከጥንት ኃጢአትን አድርጓልና። ስለዚህ ተገለጠ የእግዚአብሔር ልጅ የሰይጣንን ሥራ ሊሽር። ከእግዚአብሔር የሚወለድ ሁሉ ኃጢአት አያደርግም። ዘሩን ጸንቶበታልና ኃጢአትም ይሠራ ዘንድ አይችልም። ከእግዚአብሔር የተወለደ ነውና። በዚህ ይታወቃሉ የእግዚአብሔር ልጆች የሰይጣንም ልጆች። ጽድቅ የሚያደርግ ከእግዚአብሔር አይደለም።፩ ዮሐንስ ፫፡፬-፲።

 

                        አገዳደፍ

 

የ፯ ግድፈት ከ ቀ ጀምሮ እስከ ፐ

የ፱ ግድፈት ከተ ጀምሮ እስከ ፐ

የ፲፪ ግድፈት ከኀ ጀምሮ እስከ ፐ ነው።

 

      ፊደሉ የተከፈለበትን መንገድ ለማወቅ ከሀ እስከ ተ ድረስ ያሉት ፊደሎች ፲ ናቸው። ከኀ እስከ ደ ያሉት ፲ ፊደሎች ደግሞ በ፲ መደብ እየተቈጠሩ በደ ላይ ሲደርሱ ፩፻ ይሆናሉ። እንዲሁም ከደ ጀምሮ እስከ ፐ በመቶ መደብ እየተቈጠሩ በፐ ላይ ሲደርሱ ፰፻ ይሆናሉ። እንግዲህ ለአቈጣጠሩ ዋና መሠረት የሚሆናቸው ከሀ እስከ ፐ ያሉትን ፊደሎች የቁጥር ስማቸውን በቃል ማጥናት ብቻ ነው።

                 

                      ፩ኛ ማስረጃ

 

      የከዋክብትን አቈጣጠር ለማወቅ አስቀድሞ የፊደሎችን አጻጻፍና አዋጁን (ዘሩን) ለይቶ ማወቅ ይገባል። ለምሳሌ ፀሐዩ የሚገባውን /ጸሃዩ በሚለው ጽፈው ቢቈጥሩት ይፋለሳል እንዲሁም፤ ዓለሙን አለሙ ሠምረን ሰምረ ኃይሉን ሃይሉ ሓረግን ሃረግ መሓሪን መሃሪ ፀዳልን ጸዳል ብለው ጽፈው ቢቈጥሩት ምሥጢሩ ይፋለስና አለኮከቡ ይሰጠዋል። ስለዚህም የ፪ ሠሰ የ፪ አዐ የ፫ ሀሐኀ፣ የ፪ ጸፀ እየሙያቸውና አዋጃቸውን ጠንቅቆ ማወቅ ያስፈልጋል። እንዲሁም የፊደሎች በሙሉ የቍጥር ስማቸውን ገ፪፻፤ ተ፲ ፤ወ፷፤ ጸ፭፻፤ ነ፴፤ ሐ፫፤ፐ ፰፻፤ በ፱፤ ደ፻ እያሉ ከእነ ዘራቸው ማጥናት ነው።

 

      ለምሳሌ የሰውየውን ስም ኃይሉ እንበል ኃ ፳ በ፲፪ ሲገደፍ ፰ ይያዛል ይ ፺ በ፲፪ ሲገደፍ፣ ፮ ይያዛል። ፮ና የኃ ቀሪ ፰፣ ፲፬ ይሆናል በ፲፪ም ሲገደፍ ፪ ይያዛል። ሉ ፪ ድምር ፬ ይሆናል።

 

      የእናቱ ስም ደግሞ ብዙ እንበል ብ ፱ ዙ ፹፣ ፹፱ በ ፲፪ ሲገደፍ ፭ ይቀራል፤ ፬ የኃይሉን ጨምረን ፱ ይሆናል። ይኸውና የኃይሉ የብዙ ልጅ ኮከብ ፱ኝኛው ኮከብ ቀውስ እሳት መሆኑ ነውና ግብሩና ባሕርዩን በምዕራፍ ልናገኘው እንችላለን። እነሆ ኃይሉ በአንደኛው ፊደል ሓይሉ ተብሎ ተጽፎ ቢሆን ኑሮ ሌላ ውጤት ይሰጠን ነበር ማለት ደለዊ ነፋስ። ይህም ዋናው የኮከብ አቆጣጠር ሥራና የፊደልን ዘር ጠንቅቆ ማወቅ ይገባል።

 

      ይህን የከዋክብት አቈጣጠር ብልሐት የሰውዬውና የእናቱንም ስም በፊደሉ ዐዋጅ ቈጥረው ቀሪውን ለኮከቡ ስም እየሰጡ ከባሕርዩ ጋር ማስተካከል ግን ስምን መልአክ ያወጣዋል የተባለው ምሳሌ ለዚሁ ትምህርት ደጋፊው ሳይሆን አይቀርም። ሉቃ ፩፡፲፪

 

             የኮከቦች ቁጥርና የባሕርይ ምሳሌ።

 

፩ኛ ኮከብ ስሙ ሐመል እሳት። ምሳሌው ድብ ነው።

 

፪ኛ ኮከብ ስሙ ሠውር መሬት። ምሳሌው  ዝንጀሮ ነው።

 

፫ኛ ኮከብ ስሙ ገውዝ ነፋስ    ምሳሌው ዓጋዘን ነው።

 

፬ኛ ኮከብ ስሙ ሸርጣን ውኃ   ምሳሌው ቀበሮና ዋላ ነው።

 

፭ኛ ኮከብ ስሙ አሰድ እሳት ምሳሌው አንበሳ ነው።

 

፮ኛ ኮከብ ስሙ ሰንቡላ መሬት ምሳሌው ጉጉት አምራ ነው።

 

፯ኛ ኮከብ ስሙ ሚዛን ነፋስ ምሳሌው ተኩላ ነው።

 

፰ኛ ኮከብ ስሙ ዓቅራብ ውኃ  ምሳሌው ነብር ነው።

 

፱ኛ ኮከብ ስሙ ቀውስ እሳት ምሳሌው ጅብ ነው።

 

፲ኛ ኮከብ ስሙ ጀዲ መሬት ምሳሌው ንስር ነው።

 

፲፩ኛ ኮከብ ስሙ ደለዊ ነፋስ ምሳሌው በሬ ነው።

 

፲፪ኛ ኮከብ ስሙ ሑት ውሃ ምሳሌው ከይሲ ነው።

                  ፪ኛ ማስረጃ።

ኮከቦች በ፲፪ ቁጥር ተቀምረው ሲያበቁ እየአንድ አንዱ ደግሞ የተወሰነ ስምና ሥራ አላቸው። ይህም ሲሆን የኮከቦችን ጠባይ ለማወቅ ብቻ በሆነ  ወይም በአስፈለገ ጊዜ ነው። አለዝያስ ለተለየ ለሌላ የሐሳብ አቈጣጠር ሲሆን ለልዩ ልዩ ሐሳብ የሚቆጠርበት ከ፫ ጀምሮ እስከ ፳ኛ ፴ በመግደፍ እጅግ ሰፊ የሆነ ልዩ ልዩ የአቈጣጠርና የአገዳደፍ ብዙ ጥበብና ስልት አለውና ለወደፊቱ ልናገኘው እንችላለን። ለምሳሌ ሐሳበ አድባር-ሐሳበ ሓራ ዘመን- ሐሳበ-ፍኖት፤ ሐሳበ-ክፍል፤ ሐሳበ ሌሊት-ሐሳበ ቦታ- ሐሳበ-ወሊድ- ሐሳበ፤ ባሕርይ ሐሳበ ወርኅ-ሐሳበ ሕልም- ሐሳበ- ፊደል-ሐሳበ ዕለት-ሐሳበ መናዝል። ሐሳበ ዳዊት ሐሳበ ዓውደ ፀሐይ ሐሳበ ሰጐን ይህንና ሌላም ይህን የመሰለው ሁሉ እጅግ ሰፊና ብዙ ነው።

 

                        መደቦች።

 

ከዚህ በላይ በተሰጠው የከዋክብት ስም በባሕርይ የተዛመዱትንና ያልተዛመዱትን ለይቶ ማወቅ ያስፈልጋል። እሳት ውሃ ነፋስ መሬት ማንና ማን ናቸው? ያልተዛመዱትም እንደ ወገኖች ሁነው ሊቈጠሩ አይቻልም በሌላው በልዩ ልዩ አቈጣጠር ተጋጥመው የሚገኙት ደግሞ ከዚህኛው አቈጣጠር ጋር ያልተስማሙ ሁነው ይገለጻሉና በሚከተለው ሐሳብ አጥልቀን እናተውላቸው፤ ባሕላቸውና ጠባያቸውም እንደ እየተርጓሚአቸው  ነው።

 

      ፩ኛ መደብ የ፩ኛው ኮከብ የሐመል እሳት የባሕርይ ወገኖቹ ፬ተኛው ኮከብ ሸርጣን ውሃና ፯ተኛው ኮከብ ሚዛን ነፋስ ፲ኛው ኮከብ ጀዲ መሬት ናቸው።

 

      ፪ኛ መደብ የ፭ኛው ኮከብ አሰድ እሳት የባሕርይ ወገኖቹ ፮ኛው ኮከብ ሰንቡላ መሬትና ፲፩ኛው ኮከብ ደለዊ ነፋስ ፪ኛው ኮከብ ሠውር መሬት ናቸው።

 

      ፫ኛ መደብ የ፱ነኛው ኮከብ የቀውስ እሳት የባሕርይ ወገኖቹ ፲፪ኛው ኮከብ ሑት ውሃና ፫ኛው ኮከብ ገውዝ ነፋስ ፮ኛው ኮከብ ሰንቡላ መሬት ናቸው። ኮከቦች በአቈጣጠራቸው ተራ የባሕርይ መመሳሰልና ወገኖች ናቸው።

              የከዋከብት ባሕርያትና ሁናቴ።

     

      ለሐመል ቤተ ንጉሡ ሐመል ቤተ ንዋዩ ሠውር ቤተ ሕማሙ ወጸጋሁ ገውዝ ቤተ ዘመዱ ሸርጣን ቤተ ውሉዱ አሰድ ቤተ ደዌሁ ሰንቡላ ቤተ ክፍሉ ሚዛን ቤተ ሞቱ ዓቅራብ ቤተ ሥልጣኑ ቀውስ ቤተ ሀብቱ ደለዊ ቤተ ፀሩ ሑት።

 

      ለሠውር ቤተ ንጉሡ ሠውር ቤተ ንዋዩ ገውዝ ቤተ ሕማሙ ወጸጋሁ ሸርጣን ቤተ ዘመዱ አሰድ ቤተ ውሉዱ ሰንቡላ ቤተ ንዋዩ ሚዛን ቤተ ክፉሉ ዓቅራብ ቤተ ሞቱ ቀውስ ቤተ ሥልጣኑ ጀዲ ቤተ ንግዱ ደለዊ ቤተ ሀብቱ ሑት ቤት ፀሩ ሐመል።

 

      ለገውዝ ቤተ ንግሡ ገውዝ ቤተ ንዋዩ ሸርጣን ቤተ ሕማሙ ወጸጋሁ አሰድ ቤተ ዘመዱ ሰንጉላ ቤተ ውሉዱ ሚዛን ቤተ ደዌሁ ዓቅራብ ቤተ ክፍሉ ቀውስ ቤተ ሞቱ ጀዲ ቤተ ሥልጣኑ ደለዊ ቤተ ንግደቱ ሑት ቤተ ሀብቱ ሐመል ቤተ ፀሩ ሠውር።

 

      ለሸርጣን ቤተ ንግሡ ሸርጣን ቤተ ነዋዩ አሰድ ቤተ ጸጋሁ ወሕማሙ ሰንቡላ ቤተ ዘመዱ ሚዛን ቤተ ውሉዱ ዓቅራብ ቤተ ደዌሁ ቀውስ ቤተ ክፍሉ ጀዲ ቤተ ሞቱ ደለዊ ቤተ ሥልጣኑ ሑትተ ንግደቱ ሐመል ቤተ ሀብቱ ሠውር ቤተ ፀሩ ውዝ።

 

      ለአሰድ ቤተ ንግሡ አሰድ ቤተ ነዋዩ ሰንቡላ ቤተ ሕማሙ ወጸጋሁ ሚዛን ቤተ ዘመዱ ዓቅራብ ቤተ ውሉዱ ቀውስ ቤተ ደዌሁ ጀዲ ቤተ ክፍሉ ደለዊ ቤተ ሞቱ ሑት ቤተ ሥልጣኑ ሐመል ቤተ ንግደቱ ሠውር ቤተ ፀሩ ሸርጣን።

 

      ለሰንቡላ ቤተ ንግሡ ሰንቡላ ቤተ ንዋዩ ሚዛን ቤተ ዘመዱ ቀውስ ቤተ ውሉዱ ጀዲ ቤተ ደዌሁ ደለዊ ቤተ ክፍሉ ሑት ቤተ ሞቱ ሐመል ቤተ ሥልጣኑ ሠውር ቤተ ንግደቱ ገውዝ ቤተ ሃብቱ ሸርጣን ቤተ ፀሩ አሰድ።

 

      ለሚዛን ቤተ ንግሡ ሚዛን ቤተ ንዋዩ ዓቅራብ ቤተ ሕማሙ ወጸጋሁ ቀውስ ቤተ ዘመዱ ጀዲ ቤተ ውሉዱ ደለዊ ቤተ ደዌሁ ሑት ቤተ ክፍሉ ሐመል ቤተ ሞቱ ሠውር ቤተ ሥልጣኑ ገውዝ ቤተ ንግደቱ ሸርጣን ቤተ ሃብቱ አሰድ ቤተ ፀሩ ሰንቡላ።

 

      ለዓቅራብ ቤተ ንግሡ ዓቅራብ ቤተ ንዋዩ ቀውስ ቤተ ሕማሙ ወጸጋሁ ጀዲ ቤተ ዘመዱ ደለዊ ቤተ ውሉዱ ሑት ቤተ ደዌሁ ሐመል ቤተ ሥልጣኑ ሸርጣን ቤተ ንግደቱ አሰድ ቤተ ሀብቱ ሰንቡላ ቤተ ፀሩ ሚዛን።

 

      ለቀውስ ቤተ ንግሡ ቀውስ ቤተ ንዋዩ ጀዲ ቤተ ሕማሙ ወጸጋሁ ደለዊ ቤተ ዘመዱ ሑት ቤተ ውሉዱ ሐመል ቤተ ደዌሁ ሠውር ቤተ ክፍሉ ገውዝ ቤተ ሞቱ ሸርጣን ቤተ ሥልጣኑ አሰድ ቤተ ንግደቱ ሰንቡላ ቤተ ሀብቱ ሚዛንቤተ ፀሩ ዓቅራብ።

     

      ለጀዲ ቤተ ንግሡ ጀዲ ቤተ ንዋዩ ደለዊ ቤት ሕማሙ ወጸጋሁ ሑት ቤተ ዘመዱ ሐመል ቤተ ውሉዱ ሠውር ቤተ ደዌሁ ገውዝ ቤተ ክፍሉ ሸርጣን ቤተ ሞቱ አሰድ ቤተ ሥልጣኑ ሰንቡላ ቤተ ንግደቱ ሚዛን ቤተ ሀብቱ ዓቅራብ ቤተ ፀሩ ቀውስ።

 

      ለደለዊ ቤተ ንግሡ ደለዊ ቤተ ንዋዩ ሑት ቤተ ሕማሙ ወጸጋሁ ሐመል ቤተ ዘመዱ ሠውር ቤተ ውሉዱ ገውዝ ቤተ ደዌሁ ሸርጣን ቤተ ክፍሉ አሰድ ቤተ ሞቱ ሰንቡላ ቤተ ሥልጣኑ ሚዛን ቤተ ንግደቱ ዓቅራብ ቤተ ሀብቱ ቀውስ ቤተ ፀሩ ጀዲ።

 

      ለሑት ቤተ ንግሡ ሑት ቤተ ንዋዩ ሐመል ቤተ ሕማሙ ወጸጋሁ ሠውር ቤተ ዘመዱ ገውዝ ቤተ ውሉዱ ሸርጣን ቤተ ደዌሁ አሰድ ቤተ ክፍሉ ሰንቡላ ቤተ ሞቱ ሚዛን ቤተ ሥልጣኑ አቅራብ ቤተ ንግደቱ ቀውስ ቤተ ሀብቱ ጀዲ ቤተ ፀሩ ደለዊ ነው።

 

 

                  ፩ኛው ኮከብ ሐመል እሳት።

 

      ሐመል እሳት የእሳት ነበልባል ማለት ነው ከመጋቢት ፲፬ ቀን ጀምሮ ማታ ማታ ይወጣል ይህ ኮከብ ያለው ሰው እንደ ኮከቡ ብርሃን አእምሮው ብሩህ ነው እጅግ ኃይለኛና ደፋር ነው የአንደበት ስጦታ አለው ደግነትም አያጣም ከፍ ያለ ሐሳብ አለው ከሽምግልና ጊዜው አስቀድሞ በአለ ዘመኑ መርሳትና መዘንጋት የለውም አደርገዋለሁ ይሆንልኛል ብሎ የወጠነው ሥራና ነገር ሁሉ ይከናወንለታል ወደአሰበው ለመድረስ ብዙ መሰናክል ያገኘዋል ነገር ግን በሐሳቡ ቆራጥነት ሁሉንም በመጨረሻ ያሸንፋል።

 

      ኮከብ እሳትነቱን የሚያጠፋው የለውም አድመኛ ነው ተንኮለኛ ግን አይደለም ሴትን ይፈራል እጅግ ለጋስ ነው ተበድሮም ቢሆን ይሰጣል ወዳጅና ጠላቱን መምረጥ አያውቅም ለባልንጀራነት ዝቅተኞቹን ይመርጣል ሳያጣና ሳያገኝ ይኖራል ገንዘቡ ይመጣና ይሄዳል እጁ አመድ አፋሽ ነው ሰጥቶ አይመሰገንም ቅንዝረኛ ነው ከ፵ ዓመት በኋላ ባለፀጋ ይሆናል። ሰፊ ዝና አለው  ከብዙ ሰው ጋር ይተዋወቃል።

 

      የወለደው አይባረክለትም እስከ መግደል ድረስ ይሻዋል የሽምግልና ዘመኑን በትካዜ ይገፋዋል ምናልባትም የረጅም ጊዜ እሥራት ያገኘዋል በእልኩ ምክንያት ዕድሉን ያበላሸዋል ቂመኛና ተበቃይ አይደለም በዳኝነትና ጽሕፈት ዕውቀቱ ከፍ ያለ ነው ነገር መተቸትና ማስተካከል ያውቃል ሕልሙ የታመነ ነው ንጉሥና መኳንንት ያፈቅሩታል አፈ ከባድ ሀብታም ነው በ፬ቱ ማእዘን ሰው ሁሉ ይሰግድለታል።

 

      በዘመነ ማቴዎስ ሞት ያስፈራዋል በጥቅምት ወር ሆዱን ራሱን ግራ እግሩን ያመዋል ሥራይ ያስፈራዋል በ፲፭ና በ፳፪ ዓመቱ ክፉኛ ይታመማል በ፶ ዓመቱ ክፉ ነገር ያገኘዋል በዘመነ ሉቃስ በመስከረምና ኅዳር በሚያዝያና ሐምሌ ውጋትና ሳል ያመዋል በታመመ ጊዜ የዝግባ ቅጠል ዘፍዝፎ ይታጠብ ሙጫውንም ይቆርጥም ጋኔንና አንበሳ አጥፊው ነው ሲታመም ጽጌረዳና ሰሊጥ የእርግብ ሥጋ ይብላ መረቋንም ይጠጣ ክንፏንም ይታጠን።

 

      ሠናይ ዕለቱ ሰኞ ማክሰኞ ቀዳሚት እኩይ ዕለቱ ረቡዕ ዓርብ እሑድ ነው መድኃኒቱ በአዳል በግ ወይም በነጭ ፍየል ብራና መፍትሔ ሥራይ ለዓይነ ጥላ መርበብተ ሰሎሞንን ለማእሰረ አጋንንት አንድም ሰይፈ መለኮትን አስጽፎ ይያዝ ቀይና ነጭ በግ ይረድ ቀይ ዝርዝር ዶሮ ይረድ አምበላይ አፈሾሌ ፈረስ ይጫን ቤተ መንግሥት ንግድ እርሻ ክፍሉ ነው ቆሙ ነዊሕ ገጹ ፍሡሕ ነው ዓይኑ እንደ ኮከቡ ብሩህ ነው ፬ ሴት ያገባል ፫ ልጆች ይወልዳል አባት እናቱን አይቀብርም ነጫጭ ነገርና ከብቶች ይሆንለታል ምቀኛ እንደ ጦር ይነሣበታል ለጊዜው ልቡ ይፈራል ያመነታል የኋላ ኋላ ግን በድፍረት ተነሥቶ ጠላቶቹን ሁሉ ድል ያደርጋቸዋል።

 

      ለጊዜው ቁጡ ነው ኋላ ግን ፈጥኖ ይመለሳል ርኅሩህ ነው ጥቂት ዘመን ዘማዊነት አለበት የሴቶች በሽታ ያስፈራዋል በፊት ሀብት ያገኛል በመካከል ይደኸያል እስከ ፫ ዓመት መቅሠፍት ያስፈራዋል ከ፵ ዓመት በኋላ ግን ሀብትና ዕድሜ በብዙ ያገኛል ቀይ ነገር ሁሉ ክፍሉ ነው በቀይ መሬት ይኑር።

 

      የሴት መድኃኒ ያስፈራዋል ጠላቱ እጅግ ብዙ ነው ወደ እግዚአብሔር ጸሎት ያዘውትር ምጽዋቱና ጸሎቱ ይሠምርለታል ደዌ ያስፈራዋል ሴሰኛ ነው ሲታመም መድኃኒቱ ቀይና ነጭ የጥቁር ቡሃ በግ አርዶ ሓሞቱን ይጠጣ እሳትና ውሃ ሙላት አጥፊው ነውና ይጠንቀቅ እኩይ ወርኁ ጥቅምት በዘመነ ማቴዎስ ሮብ ወይም ዓርብ ቀን በጀምበር ግባት በ፹፪ ዓመቱ ይሞታል።

 

            ሐመል ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደሆነ።

 

      እግረ ወልሻሻ ዓይነ መልካም ናት በጥርሷ ምልክት አለባት ወደምሥራቅ ትሔዳለች ፀጉረ መልካም ደረቅ ተቀያሚ በልቧ ቂም ቋጣሪ ናት መልኳ ደማም ናት ክንዷ ጥርሷ ጠጉሯ ያምራል ወንዶች በፍቅር መኝታ ይወዷታል ልጆች ትወልዳለች በኋላ ግን ማኅፀንዋን ሾተላይ ይመታታል በሥራዋ ተመካሒ ራሷን አኩሪ ናት ቅናትና እብለት ወረትም አለባት ሆዷን ያማታል ከ፵ ዓመት በኋላ ሰውነቷ ይበርዳል ተራክቦን ትተዋለች ወደምሥራቅ አገር ብትቀመጥ ይሻላታል ዕድሜዋ ፸ ዘመን ነው።

 

                 ፪ኛው ኮከብ ሠውር መሬት

 

      ይህ ኮከብ በሚያዝያ ፲፮ ቀን በዐዜብ በኩል የሚወጣ ነው ይህ ኮከብ ያለው ሰው እጅግ ገራም ነው ምሥጢራዊ ባሕርይ አለው የአደረገው ነገር ሁሉ አይታወቅበትም ምክንያቱም ኮከቡ ድብቅ ወይም ሥውር ስለሆነ ነው።

 

      እጅግ ጌጥ ይወዳል ገንዘብ በጣም አይገባውም እንጂ ገንዘብ ማውጣት ጭንቁ ንፋግ ነው ሃብቱ ሥውር የኋላ ኋላ ነው በሰውነቱ ተመካሒ አፈጻድቅ ነው ቅናትና ምቀኝነት አሉበት ሲያውቅ አለ ዓዋቂ ይመስላል አንደበቱ ዝግተኛና ልዝብ ነው ቀልድና ጨዋታ ዕድሉ ነው እርሻ ንግድ ቤተ መንግሥት ይሆንለታል ሰላማዊ ነው ኩሩ መስሎ ይታያል ከሰው ጋር በቶሎ አይላመድም በቤተ ሰዎቹ ላይ ኃይለኛ ገዥ ነው ከበታቹ ያሉትን ያጠቃል፤ ፍርሃት አያውቅም ልበ ሙሉ ነው ወረተኛና ውለታ ቈጣሪ ብልህ ነው ነገር ግን ሰው አያምነውም። እርሱም ሰውን አያምንም ለሁሉ ጠርጣሪ ነው።

 

      ከአሰበው አይመለስም የሰው ምክር አይቀበልም ራሱን ከፍ አድርጎ ገማችና እኔ እበልጥ ባይ ነው በተግባሩ ሁሉ አምላክን ይለምናልና ይረዳዋል ጠላቶቹን ሁሉ በጸሎቱ ድል ያደርጋቸዋል በኋላ ዘመን ገንዘብ ያልቅበታል በጥቂት መጠጥ ይሰክራል ሆዳም ነው በመብልና መጠጥ ሥራይ ያስፈራዋል የሚያደርጉበትም ዘመዶቹ ናቸው ወደ ዘመነ እርጅናው የዓይን ሕመም ያስፈራዋል በጋብቻው የታመነ ነው የተባረኩ ልጆች ይወልዳል ዕድሉ በአንድ ድንገተኛ ነገር ነው ፬ ልጆች ይወልዳል መሐላ አይሆነውምና በእውነትም ቢሆን አይማል።

 

      ክፍሉ ነጭና ቀይ መሬት ነው መሸጥ መግዛት መለወጥ ሹመት ክፍሉ ነው ማስተዳደርና ሥርዓት ያውቃል ቆላ አገር አይሆነውም ደጋ ይስማማዋል በዘመነ ማርቆስ ጥቅምትና ግንቦት ሩቅ አገር አይሒድ ቅሥፈት ያገኘዋል ከሚወልዳቸው ልጆቹ ፩ዱ ሕመምተኛ ይሆናል ሰው ሲሞት ሬሳ አይገንዝ ታስሮ ይፈታል በዘመነ ማርቆስ በመጋቢት ወር ሹመት ያገኛል በዘመነ ማርቆስ ሩቅ አገር አይሒድ ጥቅምትና ግንቦት ቤት አይለውጥ ቅሥፈት ያስፈራዋል ሰውነቱ ኃያልና ደፋር ነው እንደ ዓይነት እያደረገ ያመዋል። ሆዱ እንደ ሥራይ  ይገለባበጥበታል ጥሬ እርጥብ ሥጋ አይወድለትም ጠብሶና ቀቅሎ ይብላ ቅናትና ምቀኝነት አሉበት ተመካሒ ሕልሙ እሙን ነው።

 

      ጋብቻው አሰድ አቅራብ ኅብሩ ሚዛን ቀውስ ሐመል ነው እኩይ ዕለቱ ረቡዕ ዓርብ እሑድ ነው የዓርብ ቀን ያስፈራዋል ነጭና ቀይ አርዶ በድሙና በፈርሱ ይታጠብ በ፱ዓመቱ ያመዋል በ፵ ዓመቱ ግን ሞት ያስፈራዋል ከወንጌለ ዮሐንስ ወሀሎ ፩ ብእሲ የሚለውን አጽፎ ይያዝ ከበሽታ ሁሉ ለጥፋት የሚያደርሰው ዋና ፀሩ ተስቦ ነው ለዚህ መጠበቂያው ቢሆን በሚዳቋ ቢታጣ ግን በነጭና ቀይ የፍየል ብራና አቅዳፌር አጽፎ መያዝ ነው።

 

      የሚመለከቱት ዛሮች ጢሞቴዎስና ብር አለንጋ ከውላጅም ደም ቀለቡና ዋስ አጋች ናቸው ራሱንና ዓይኑን ልቡን እየከፈለ ያመዋል በግራ ዓይኑና በግራ እግሩ ምልክት አለበት ሴት ጋኔን አለችበት ሌሊት በሕልሙ ታስደነግጠዋለች ሌሊት ልብሱን ታስጥለዋለች ምቀኛ ሆና ሃብቱን ትዘጋበታለች እርሷን ለማስለቀቅ የሚበጀው ጊዜዋ ጉመሮ ዕጣን የጅብ አር ዋግራ ድብርቅ አልቲት የዶሮ ላባ እነዚህን በአንድነት ይታጠን ስመ አምላክና ወንጌል ማርቆስ ድርሳነ ሚካኤልንም በሌሊት ውሃ እየአስደገመ ከእነዚያ መድኃኒቶችም በውሃው ጨምሮ ይታጠብ።

 

      ሠናይ ወርኁ ታኅሣሥ እኩይ ወርኁ ጥቅምት ጥር ግንቦት ነውና ይጠንቀቅ። ቁርጥማት ወይንም ቂጥኝ ከጥቁር ሴት ያስፈራዋል መድኃኒቱ ጣዝማ ሰሊጥ ጊዛዋ በማር ይዋጥ። ከልከሎሳ የሚባል ጋኔን በተወለደ ዕለት አይቶታልና በታመመ ጊዜ ያብዳል። መድኃኒቱ ነጭ በግ ቀይ የበሬ ቀንድ አርባ ቀን ያልሞላው የመቃብር አፈር በአንድነት አሳርሮ ውኃ ባልነካው ቅቤ አድርጎ በ፬ ማእዘን መንገድ ላይ ቁሞ ይቀባ ከእራሪው በጠጅ አንፍሮ ፫ ቀን ይጠጣና ይለቀዋል።

 

      በእግሩ ቁርጥማት ይሰማዋል በራሱ በልቡ በሆዱ በሽታ ይገባበታል ለዚህ ሕመም መድኃኒቱ፤ ዋግራ ድብርቅ አልቲት ሮብ ቀን ሰብስቦ ከጥቁር ስንዴ ጋር በጨው አንፍሮ ለቀይ በግ ፯ ቀን ማብላት ነው ከዚህ በኋላ በጉን አርዶ በደሙ ታጥቦ ሥጋውን ቀቅሎ መረቁን በስንዴ እንጀራ እየፈተፈተ ይብላ ከእህልም ስንዴ ግጥሙ ነው ከመረቁ ይጠጣ ቀይ ዶሮ ወሰራ ጭዳ ይበል። ሞቱ በዘመነ ማርቆስ በ፸ኛ ዓመቱ በወርኃ ጥቅምት ሮብ ቀን ነው።

 

 

            ሠውር መሬት ያላት ሴት የሆነች እንደሆነ።

 

ዕውር ደም ይመታታል ዓይንዋ ቀላ ያለ ጥሩ ነው ቀናተኛ ናት አመንዝራት አለባት ባሏን በእጁ ነፍስ እስኪያሳልፍ ድረስ ታስቀናዋለች ቅዳሜ ቀን አይሆናትም ደም ከፈሰሰበት ሥፍራ አትድረስ በመቃብር የእምኖር ከልከሎሳ የእሚባል ጋኔን ይፃረራታል ግራ ዓይኗን ያማታል ሆዷን እያላመጠ ደም እንደ ውኃ ይፈሳታል እግሯን ይቈረጥማታል ሰኔና ጥቅምት አይሆናትም አቅዳፌር በእንስት ምዳቋ ብራና አስጽፋ ትያዝ። የጥቁር ገብስማ ዶሮ ጭዳ ብላ ሥጋውን ሠርታ ኮረሪማ ሰልቃ በበላዩ ነስንሳ ሥጋውን ትብላ መረቁንም ትጠጣ። ከዚህ በኋላ የደም ጽሑፍና አቅዳፌር ጨምራ ትያዝ ሰውነቷ በፊቷ ደንዳና ነው ፀጉሯ ልስልስ ነው ስስት አለባት ቁም ነገርና ሃይማኖትም ይገኝባታል።

 

                ፫ኛው ኮከብ ገውዝ ነፋስ።

 

      በግንቦት ፲፬ ቀን የሚወጣ ኮከብ ነው ነገሩ ዶርዝ ጥንድ ነፋስ ማለት ነው በቀበሮና ዋላ ይመሰላል ይህ ኮከብ ያለው ሰው ጸጥታ የለውም ብልሕ መሠሪ  ጥዑመ ልሳን ራሱን ጠባቂ ርጉዕ ድምጹ ከበድ ያለ ቀልድና ዋዛ ዐዋቂ ነው። ነገር ሁሉ በቶሎ ይገለጽለታል በልቡ ፍርሓት የለውም በሰው ነገር ዘልሎ መግባት አይወድም ባልንጀራውን አያምንም በትንሽ ነገር አዝኖ  በትንሽ ነገር ደግሞ ይደሰታል ምሕረት የሌለው ቂመኛ ነው መሐላ ይደፍራል አክብሩኝና ወድሱኝ ባይ ነው መኳንንትና ጌታ ይወደዋል ጥቂት እርግማን አለው።

 

      እኩያው ካልሆኑት ከበላዮቹ ጋር ባልንጀራነት  ይገጥማል ግን አይጠቅሙትም ብዙ ሰምቶ ጥቂት ይናገራል ደስታውንና ኀዘኑን ለሰው አያካፍልም ከአንገት በላይ ይናገራል ለሰው መሸንገልና ማታለል ዕድሉ ነው ሳይታወቀው ይሰጥና እንደ ገና ይጠጠታል ሁሉን ሰው ይጠረጥራል አሽከሮቹና ዘመዶቹ ጠላቶቹ ይሆናሉ ስሙ በክፉ ይጠራል ከሚስቱ ብቻ ይወልዳል ከሌላ ቢወልድ አይባረክለትም መስጠት እንጂ መቀበልን አይወድም ዕቡይ ምቀኛውም ብዙ ነው እርሱም ለሰው ምቀኛ ነው ቢታመም ፈጥኖ ይድናል ዓይነ ደረቅና ደፋር ነው።

 

      በባዕድ አገር በዘመነ ማርቆስ ሹመት ያገኛል ዕድሉ በአልተወለደበት አገር ነው ወደ ምሥራቅ ሄዶ መኖር ይሆነዋል ንግድ ክፍሉ ነው። ከሃምሳ ዓመት በኋላ ባለፀጋ ይሆናል ጾምና ጸሎት  ይሠምርለታል በዘመነ ማቴዎስ ታሥሮ ይፈታል ነጭ ነገር ክፍሉ ነው ዋገምት ይታገም ጤና ያገኛል በ፯ ዓመቱ መቅሠፍት ያስፈራዋል ሠናይ ወርኁ ታኅሣሥ መጋቢት ሚያዝያ እኩይ ወርኁ ሰኔ ነሐሴ ጥቅምት ነው በ፳ና በ፵፭ ዓመቱ ደዌ ያስፈራዋል ቀይና ነጭ ይረድ የፋኑኤልን ሰላምታ አስጽፎ ይያዝ የሉቃስንና ዮሐንስን ወንጓል አስነብቦ ፯ ቀን ይጠመቅ። ዓይኑንና ልቡን ያመዋል ፈጣን እንዲሆን የአህያ ሰኰና በግራ ክንዱ ይያዝ ዘማዊነት አለው ግራ እግሩን ብረት ይወጋዋል ፌራና ንዳድ ያስፈራዋል እርሻም ይሆንለታል። ቁመቱ ድልድል መንጋጋው ትልልቅ ነው በሴት ምክንያት ትዳሩ ይሰናከልና እንደገና ይታረቃል።

 

      ዓይነ ደረቅ ኃይለኛ ጋኔን ክንዱን ትከሻውን ያመዋል ዋስ አጋች የሚባል ዛር በሕልሙ እየተመላለሰ ይጠናወተዋል መድኃኒቱ እንኮይና ቅቤ በወይን ቅጠል አቡክቶ ይጠጣ ቁርጥማት ያመዋል ጉመሮ ጅብራ አውጥ በአዲስ ዋንጫ ዘፍዝፎ ይታጠብ። ራሱን ሆዱን ጉሮሮውን ያመዋል ከዛር የተወለደ ጋኔን ስሙ ረዋዲና ጐዳሌ የሚባል ይመለከተዋል ለቁራኛው ዓይነት ይወጣለታል ጫማውንና ጉልበቱን ይቈረጥመዋል ወሰን ገፊ የሚባል ዛር ሳይወታቅ ተደርቦ ይፃረረዋል በሽታው የሚብሰው በሰኔ ነው ለዚህ መድኃኒቱ የዝግባ ሙጫና የመስክ አበባ መታጠን ነው ይህ ኮከብ ያለው ሰው ጭዳው በጥቅምት ወር ነጭ ፍየልና ነጭ ዶሮ ነው፤ በነጭ ፍየል ብራና አልቦ ስምና ከዳዊትም አንሣእኩን አስጽፎ ይያዝ ቀኝ እግሩ እንዳይመነምን ያስፈራዋል የዚህ ፈውሱ የጠምበለል ቅጠል ጉመሮ ቀርሻሽቦ የበረሃ ግሜ ሥረ ብዙ የእነዚህን ሥሮችና የርግብ ሥጋ ፩ ላይ ሰልቆ አዋሕዶ በሌሊት ውሃ ዘፍዝሮ ጧት ጧት እስከ ፯ ቀን ድረስ ይታጠብ ቢጠጣላትም ደግ ነው።

 

      ለዚህ ኮከብ ፀሮቹ ከመሬት ጀዲ ከውሃ አቅራብና ሸርጣን ናቸው፤ ኮከብ ክፍሉ ቀውስ አሰድ ሰንቡላ ሑት ነው። ከዘመን ሉቃስ ከወርም ጥቅምትና ሰኔ ከቀንም ረቡዕና ዓርብ አይሆነውም ሠሉስና ሐሙስ ግጥሙ ነው በ፹ ዓመቱ ሮብ ቀን በውጋት ይሞታል።

 

      ገውዝ ነፋስ ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደሆነ።

 

      በሰው አገር ትከብራለች ትልቅ ጌታ ከሆነ ሰው ወንድ ልጅ ትወልዳለት ፊቱ ዝምተኛ ኋላ ግን ምላሷ ተናጋሪ አንደበቷ ሰው ደፋሪ ትሆናለች። የኋላ ኋላ ጥቂት የደም ሕመም ያገኛታል ዓይነ ገብ ናት  እጀ ሰብእ ይፃረራታል። ልቧ ለሰው ይራራል ዓይንዋ ቀላ ቀላ ያለ ነው ጥቂት ዘመን በዘማዊነት ትታማለች ኋላ ግን ሥጋዋ ቶሎ ይበርዳል የሰው ምክር ተቀባይ ናት በሆዷ ብርቱ ቂም ያዥ ናት የቤትዋ ሥርዓት ሞቅ ሞቅ አይልም ከአንገቷ በታች ደም ግባታም ናት ሀብት አይጐድልባትም ሰውነትዋ በራድ ነው በኵስኵስትና ሰሐን ንግድ ይሆንላታል። ዕድሜዋ ፷ ዓመት ነው።

 

                 ፬ኛው ኮከብ ሸርጣን ውሃ

 

      ይህ ኮከብ በሰኔ ፳፩ ቀን ከ፫ ኮከቦች ጋር በምሥራቅ በኩል በዶሮ ጩኸት የሚወጣ ነው።

 

      “ሸርጣን ነገረ ሰይጣን” ይባላል በጃርትና በአጋዘን ይመሰላል ሸርጣን ውሀ ማለት የምንጭ ውሀ ማለት ነው። ይህ ኮከብ ያለው ሰው ባሕርዩ ልዝብ ጭምትና አስተዋይ ነው። ከአንገት በላይ ሰውን ይወዳል ለትልልቅ ነገሮች ይታገሣል በትንሽ ነገር ይቆጣል ፍቅሩን አይጨርስም ከዳተኛና ውሸታም እምቢተኛ ነው። ፈጥኖ ሰውን ይወዳል ፈጥኖም ይጣላል ትልቅ ኃዘንና ደስታ በየጊዜው ይለዋወጥበታል ምክር ያውቃል ገንዘብ ወዳጅ ነው ራሱን ሲላጭ ይታመማል ሰውን ደላይ ወረተኛና ሸፋጭ ነው ተስፋ አይቈርጥም በስንት ተአምራት ከብዙ መከራ ይወጣል በነገረ ዝሙት የተነሣ እሥራትና ግርፋት ያገኘዋል ሥራ ወዳጅ ነው ገንዘብ በማጭበርበር በስጦታ በውርስ ይገባለታል እንዲሁም ይወጣል አይቆምለትም ከዘመዶቹ ጋር ጠብና ክርክር ያበዛል ነፍናፋ ኩርፍተኛ ነው መሓላ ይደፍራል ንግድና እርሻ ክፍሉ ነው ተንኰሉና መዘዙ ክፉ ነው ከፍ ባለ ወንጀል ተከሦ አደባባይ ላይ ለፍርድ ይቆማል ደረቅና እልከኛ ነው የሰው ምክር አይሰማም ለሰውም ደግ አይመክርም ቅንዝረኛ ነው ተንኮለኛ ነው። ያመሰገነው ሰው ብቻ ያሞኘዋል የተናገረውን ሁሉ አዎን በሉኝ ባይ ነው ቅኔ ጽሕፈት ተኵስ በገና ግጥም ዕድሉ ነው ጥቂት ጊዜ እስራት ያገኘዋል። በሸንጎና ጉባኤ ሕዝብን ለማስረዳት በቂ ንግግር አይሆንለትም። ድምጹ ጉልህ ነው በዓይኑና ደረቱ በክንዱና በእምብርቱ ላይ ምልክት አለው ቂም የለውም ይቅር ባይ ነው የሰውን ብልሓት ለማስቀረት ንቁ ነው ኑሮውን ሁሉ ሚስቱ ታዝበታለች በሚስቱ ምክንያት ከዘመዶቹ ጋር ተጣልቶ ይለያያል መጠጥ ያበዛል ስካር ያሸንፈዋል። ገንዘቡን ሁሉ ልጁ ያባክነዋል ልጅ ይሞትበታል። ለዚህ ኮከብ ጸሮቹ ገውዝ ሰንቡላ ቀውስ ሑት፤ የክፍል ኮከቦቹ ጀዲ ሚዛን ሓመል ናቸው።

 

      ከዘመን ዮሐንስ ከወር ኅዳርና ታኅሣሥ ከቀንም ማክሰኞ ዓርብ እሑድ ያስፈራዋል ከ፷ ዓመቱ በኋላ ድኻና ሴሰና ይሆናል ባርያ ዛር ያመዋል በልቡ ሳል ያድርበታል መነኩሴ ይሆናል ሥራይ ያስፈራዋል እሑድ ቀን ይጠንቀቅ ራቅ ካለ አገር አይሂድ ቀይ ሴት አያግባ የሰጠችውንም አይቅመስ በግራ እግሩ ምልክት አለበት በማርቆስና በዮሀንስ ይታመማል ሠናይ ወርኁ ሰኔ እኩይ ወርኁ ታኅሣሥ ነው በታመመ ጊዜ መድኃኒቱ የርግብና የፌቆ ሥጋ ከሰሊጥ ጋር አሠርቶ ይብላ መረቁንም ይጠጣ ጠጕራቸውንም አሳርፎ ይታጠን በ፵ ዓመቱ ጋኔን ዓይቶታልና ደም ያገኘዋል ራሱን ወገቡን ያመዋል በፌቆ ብራና መስጥመ አጋንንትን አስጽፎ ይያዝ።

 

      በግራ ጐኑ ደዌ ያድርበታል የዛር ውላጅ በአፍንጫው ደም ያነሥረዋል በሕልሙ ያስደነግጠዋል በ፲ ዓመቱ ጉሮሮውን ያመዋል መብረቅ ያስፈራዋል ማእሠረ አጋንንትና አስማተ ሰሎሞን አስጽፎ ወንጌለ ዮሐንስንም አስነብቦ ይጠመቅ። የጥቁር ወሠራ ዶሮ ቡሀ በግ ይረድ። ሠናይ ዕለቱ ሰኞ ሐሙስ ቅዳሜ እኩይ ዕለቱ ዓርብ ሮብ እሑድ። ሠናይ ወርኁ መስከረም ጥቅምት ጥር የካቲት እኩይ ወርኁ ኅዳር ሚያዝያ ሐምሌ ነው የሱፍና የኑግ ቅባኑግ ከሰሊጥ ጋር ይጠጣ። በምዕራብና ምሥራቅ ጠበል ይጠመቅ።

 

      በየካቲትና ታኅሣሥ ለሞት የሆነ ብርቱ ጦርነት ያስፈራዋል። ቅዳሜ ቀን ደም አያውጣ መድኃኒቱም አይጠጣ የዘመዶቹን ገንዘብ ይወርሳል የሴት ዓይን ያስፈራዋል ሆዱን ዓይኑን ያመዋል በጥር በየካቲት ቁስል ያገኘዋል በምንጭ በገደል የምትቀመጥ ሴት ጋኔን ትመታዋለች እርስዋ ከዘማዊነቱ የተነሣ እንደ ቅናት አድርጋ ራሱን ሆዱን ልቡን እየቀሰቀሰች በቀኝ እግሩ እንደ ቁርጥማት ትገባበታለች ብልቱን እንደ ሽንት ማጥ አድርጋ አሳብጣ ታመዋለች በሕልሙ በድቀት ሥጋ ትገናኘዋለች ለዚህ ሰው መድኃኒቱ የጥቁር ገብስማ ዶሮ በራሱ አዙሮ ያኑር ጉመሮ ጊዜዋ ጠምበለል ሥራቸውን ወቅጦ የዶሮዋን ክንፍ ጨምሮ ይታጠን ከእነዚህም ሥሮች በሌት ውሃ ዘፍዝፎ ፫ ቀን ይታጠብ አስማተ ሰሎሞንና አቍያጽያትን አስጽፎ ይያዝ። በ፷፱ ወይም በ፸ ዓመቱ በዘመነ ዮሐንስ ሮብ ወይም እሑድ ቀን በተፊአ ደም ይሞታል።

 

            ሸርጣን ውሀ ኮከብ ይላት ሴት የሆነች እንደሆነ።

 

      ዓይነ መልካም ጥርሰ መልካም ናት ቤተሰብ አይስማማትም ነገር ታበዛለች ባልዋን ፈትታ በሰው አገር ትኰበልላለች መድኃኒትና ደም ያስፈራታል ራስዋን ዓይኗን እጅዋን ሆዷን ያማታል ሐር ማተብና ብር ቀለበት ከአንገትዋ ባይለያት መልካም ነው የጋላ ዛር ሌሊት ያስተዳድራታል ሰንበትን አቦን ሥላሴን ተጠንቅቃ ታክብር ጠቋር በዶስ የሚባሉ ዛሮች ይመለከቷታል መድኃኒትዋን የጥቁር ገበሎ ራስ ፩ በቀል ፍየለ ፈጅ ጥቁር ኢዮባን መርበብተ ሰሎሞንን በጥቁር ፍየል ብራና ፩ነት ጽፈህ አስይዛት ጋኔን ይጸናወታታልና በሜዳ ከወንድ ጋር እንዳትገናኝ ትጠንቀቅ።

 

                  ፭ኛው ኮከብ አሰድ እሳት።

 

      ይህ ኮከብ በሐምሌ ፳፮ በመስእ በኩል የሚወጣ ነው አሰድ እሳተ የመብረቅ እሳት አሰድ የያዘውን አይሰድ። አሰድ ፀሐይ ዕንቈ ባሕርይ ይባላል። በአንበሳ ይመሰላል። ይህ ኮከብ ያለው ሰው የፊቱ አወራረድ አንበሳ ይመስላል ቁመቱ ድልድል ነፍሱ ንጹሕ ከእናቱ ማኅፀን የተመረጠ ልቡ የዋህ ገጹ ፍሡሕ ጥርሱ ፍንጭት ነው። ትልቅ ግርማ የዓይን ኃይል አለው ጠላቶቹ ሲያዩት ይፈሩታል ይለማመጡታል በሴራ የመከሩበትን ሁሉ ጊዜ ያፈርስባቸዋል ማናቸውንም ነገር ቢፈልግ ለማግኘት ይቻለዋል የገንዘብ ስሱ ነው ጥቂት ነገር ይበቃ አይመስለውም ቁጡ ነው ቶሎ ይመለሳል ጠላት ይበዛበታል ግን አይሸነፍም።

 

      እጅግ ምቀኛና ቀናተኛ  ነው የሰውን ነውር ያወራል ኃጢአቱ ብዙ ነው በምጽዋት ይሰረይለታል ዘማዊ ነው ከዝሙት ብዛት የተነሣ ዓይኑን ያስፈራዋል ይሉኝተኛና አንደበታም ነው መንፈሳዊ መስሎ መታየትን በሰው መመስገንና ውዳሴ ከንቱን ይወዳል። በእጁ ጥፍር ከላይ ወደታች ጥቁር መሥመር አለው ድንገተኛና አደገኛ ነው። ምሥጢርና ሴራ ክፍሉ ነው ስሙ በክፉ ይነሣል ውስጠ ደግ ወዳጁን ጠቃሚ ነው ዘመዱን አይጠቅምም ገንዘቡን ለባዕድ ያባክናል ገፊ ነው ዘመዶቹና ወዳጆቹን ከሸኘ በኋላ ብቻውን ይቀራል።

 

      ጊዜ ካነሳው ጋር ወዳጅነት ይገጥማል ገንዘቡን ከሰው ገንዘብ ጋር ማቀላቀል አይሆንለትም ኃይለኛ በኃይሉ ተመካሒ ነው እርሻና ቤተ መንግሥት ክፍሉ ነው ሹመት ያገኛል ርኩስ ከብት ላም ንብ ይሆንለታል ፫ ሚስት ያገባል ከሦስተኛይቱ ደግ ልጅ ይወልዳል ሐሙስ ቀን መሰናክል ያገኘዋል ሁለት ጊዜ እሥራት ያገኘዋል ግን በቶሎ ይፈታል ለጋስ ነው የትም ቢሔድ የሰው ፍቅር አለው ሰጥቶ አይመሰገንም ጠላቱን ይወዳል በሸንጎ ሲቆም ረትቶ ይገባል ሰውነቱን እያሳበጠ ያመዋል ኮሶም እየደፈነ አያሽረውም እግዚአብሔርን ፈሪ ዓይነ ቅንዝረኛ ነው ጥቁር በግና ነጭ ዶሮ ይረድ ሰሊጥ ዓሣ ኤፍራን ቀለም በ፩ነት አሰርቶ ይብላ መረቁንም ይጠጣ ከፀጉሮቹም ፯ ቀን ይታጠን።

 

      ከእዳሪ ውድቀት የተነሣ ሕመም ያስፈራዋል ዓይኑን ራሱን ያመዋል ዓርብና ቅዳሜ ከሰውነቱ ደም አያጣውም መድኃኒት አይጠጣ መንገድም አይሒድ የሰው ገንዘብ አደራ አያስቀምጥ አጥፊው ነው ሚስቱ በደም ትሞትበታለች ሴት ጋኔን በወገቡ በልቡ እየገባች ታመዋለች ፫ ጊዜ ገንዘቡ ይጠፋበታል። እርሱም እየታሠረና እየተፈታ ይኖራል ሢሳይ አያጣም ገንዘቡም ለዘመዶቹ መስጠት አይወድም ከሚሰጥ ቢሰርቁት ይወዳል ውሸቱን ነገር አሾክሽኩልኝ ይላል ልጆች ይወልዳል ጥቂቶች ይሞቱበታል ያልታወቁ ሰዎች ነጥቀው እንዳያጠፉት ያስፈራዋል። በሐፍረቱ ላይ ምልክት አለበት በእግሩና በእራሱ የሰው ዓይን ያስፈራዋል ጫጫታ የምትባል ዋናዋ የዛር ውላጅ ትሸምቅበታለች በዓይኑና በብልቱ ትገባዋለች ሌሊት በሕልሙ ትገናኘዋለች ቀኝ እግሩን ጉልበቱን ወገቡን ራሱን ዓይኑን ልቡን እየላሰች ታመነምነዋልች ለዚች መድኃኒትዋ የቍልቋልና የሎሚ ተቀጽላ የአሜራ ሥር ከርቤ ጨምሮ አንድነት በአዳል በግ ብራና በነጭ ጨርጨቢ አጽፎ ከነዚህ መድኃኒቶች ጋራ ፩ ላይ ይያዝ።

 

      የመኖሪያ ክፍሉ ከተማ ቤተ መንግሥት ነው ማቴዎስና ማርቆስ ተከታታይ ዘመኖች ክፍሉ አይደሉም በነዚህ ዘመኖች ይህን ጽሕፈትና እነዚያን ተቀጽላዎች የነጭ ወሰራ ዶሮ ደም እየነከረ በዓመት በዓመት እያነገሠ ይያዝ የውሃ ሙላት ያስፈራዋል ቅዳሜና እሑድን አክብሮ ተጠንቅቆ ይዋል። ቀይ አረመኔ የሆነች ጋላ ሴት ያግባ ይወልዳል ይከብራል። ኮከብ ግጥሙ ሠውር አቅራብ ደለዊ ነው። ፀሩ ሑትጀዲ ሸርጣን ነው። ማዕከላይ ሰንቡላ ቀውስ ገውዝ ናቸው። መልካም ወራቶቹ ታኅሣሥና የካቲት ክፉ ወሩ ግንቦት ክፉ ቀኑ ዓርብ ነው። በ፲ በ፳፬ በ፴ በ፵ ዓመት ያስፈራዋል። በማቴዎስ ወይም በማርቆስ በሰኔ ወይም በነሐሴ ዓርብ ቀን በ፸፱ ዓመቱ በድንገት ይሞታል።

 

            አሰድ እሳት ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደሆነ።

 

      መኳንንት ያፈቅረዋታል አካልዋ ንጹሕ ጥርሰ መልካም ናት ዘማዊነት አለባት ጥቁር ሰው ክፍልዋ አይደለም አጥፊዋ ነው የቂጥኝ ዕግል ያስፈራታል በመስከረምና ጥቅምት ዓርብና ቅዳሜ ቀን ሩቅ አገር አትሒድ ትጠንቀቅ ፩ ከወለደች በኋላ ማኅፀኗ ቶሎ ፍሬ አይዝም እንደ መካንነት ይከጅላታል ወንድ በመኝታ ያፈቅራታል  የቤት አያያዝ ታውቃለች መብልና መጠጥ ትችላለች ለቤተሰብ መልካም ደግ የዋህ ናት የጥቁር ሰው ዓይን ያስፈራታል የእጀ ሰብእ መድኃኒትና ጨርጨቢ አስጽፋ ትያዝ።

 

               ፮ኛው ኮከብ ሰንቡላ መሬት።

 

      ይህ ኮከብ በመስከረም ፯ ቀን ከ፪ ከዋክብት ጋራ ከሌሊት በ፯ ሠዓት ከወደ ፀሐይ መግቢያ የሚወጣ ነው። ሰንቡላ መሬት ቅልቅል መሬት ማለት ነው ሰንቡላ የሰው ይበላ ይበላል በጉጉት አሞራ ይመሰላል።

 

      ይህ ኮከብ የአለው ሰው በብዙ እንኳ ባይሆን ከግምባሩና ከቅንድቡ አወራረድ የዓይኑ ቅርፅ የጉጉት ምሳሌ ይገኝበታል። ሌሎች የደከሙበትን ገንዘብ ለመውሰድ ሰብሳቢ ዕድል አለው ምክሩ ዘሊቅ ነው ለሰው ይጠቅማል ኑሮው በአገባብ ነው ውሸታምና ጉረኛ ነው መጀመሪያ ይደነግጣል እየቈየ ግን ደፋርና ልበ ሙሉ ይሆናል የተገባ ምክር የነገር ምላሽ ያውቃል በተወለደበት አገር አይኖርም በቀይ ቦታ ይኑር ነጭ ነገር ክፍሉ ነው ከዘመዶቹ ጋር አይስማማም በነገር አይረታም ሕልሙ እሙን ነው ቶሎ ይደርሳል ሲሳየ ብዙ ነው ሰውን ማሞኘት ይችላል አጭበርባሪና ብልጥ ነው ክፍሉ ከተማ ነው ገጠር አይሆነውም ሹመት ያገኛል ሳቅ ያበዛል እግዚአብሔርን ያምናል ጸሎቱ ሥሙር ነው በጊዜ ወደ ቤቱ መግባት አይሆንለትም ያልደረሰበትና የማያውቀው አገር የለም ፊቱን ትክ አድርገው ቢያዩት አይችልም ፊቱን ያዞራል ከትልቅ ሰው ጋር ሲነጋገር ይጃጃል የአሰበውን ትቶ ያላሰበውን ይናገራል የሰው መውደድ አለው ስጦታና ሽልማት ለማግኘት ዕድላም ነው ተልኮ ጉዳይ ማከናወን ይሆንለታል በዘንግ ቁሞ አይችልም ተቀምጦ ሲመክር ዓዋቂ ነው።

 

      ሰፊ ዝና አለው ከሰው ጋር በቶሎ አይላመድም ሰላማዊ እንኳ ቢሆን ነገር ወደ አለበት ፈልጎ ይገባል ያሰበውን ትቶ ያላሰበውን ይናገራል ወዲያው ደግሞ ይጠጠታል በብዙ ነገር ዕድለኛ ነው ነገር ግን ዕድሉን በገዛ ራሱ ያጠፋዋል ወደ ኋላ ጊዜው ጥቅሙን አባራሪ እንጀራውን ገፊ ይሆናል የሕፃን ሽማግሌነቱን በወራዳነት ይለውጠዋል የጠላቶቹን መውደቅ ያያል። ቅንዝረኛ ነው። ኃይል እልከኛ አትንኩኝ ባይ ቶሎ ተቈጭ ነው ነገር ግን አጭሮ አይጣላም ልጆች ይወልዳል ሰውን ማማት ይጠላል ጠላቱ ብዙ ነው ፊቱ ክፍት ቀላል ድምጹ ከባድ ሆኖ ብትን ነው። ሴት መድሃኒት ታበላዋለች በ፳፯ ዓመቱ መቅሠፍት ያስፈራዋል ጭኑን ይቆረጥመዋል እራሱን ብልቱን ወገቡን ሆዱን እየነፋ ያመዋል። መድኃኒቱ ነጭ ወይም ቀይ በግ አርዶ በደሙና በፈረሱ ይታጠብ ዓሣና ሰሊጥ በዛጐልማ ዶሮ አሠርቶ ይብላ መረቁንም ይጠጣ።

 

      ለሆዱ በሽታ ደግሞ የበግ ላትና ደረቅ ጠጅ ቁንዶ በርበሬ ኤፍራን ቀለም የአሞሌ ጨው ፩ ጽዋ ቅባኑግ ነጭ ሽንኩርት በቶፋ መርጎ ፫ ቀን ከበላዩ እሳት አንድዶ ማር እየበላ ይጠጣው። በነጭ በግ ብራና ጸሎተ ንድራ ትምህርተ ኅቡዓትና መስጥመ አጋንንትን አስጽፎ ይያዝ። የምስርችና የፍየለ ፈጅ የግዛዋና የቋራ አረግ በአዲስ ቅል ዘፍዝፎ ኪዳንና ትምህርተ ኅቡአትን አስቀድሞ ይታጠብ።

     

      ከዘመን ማርቆስ ከወር ታኅሣሥና መጋቢት አይሆኑትም በጥርና ሰኔ ድንገት በሽታ ያገኘዋል ለዚህ መድኃኒቱ ጭቁኝ ነጭ ሽንኩርት ቁንዶ በርበረ ጫት ቡና ፩ነት እያፈላ እስከ ፯ ቀን ይጠጣ ዕጣን ያጢስ ኮከቡ አምልኮ ይወዳል የቀይ ከላድማ ፍየል ወይም ቀይ በግ ጭዳ ያድርግ። ከሚፈላው መድኃኒት አትርፎ በቀይ ዶሮ ደም አጥምቶ (ነክሮ) ክንፉን ጨምሮ ፫ ቀን ይታጠን። በበግ ብራና ማእሰረ አጋንንትና ፬ቱ ኤኮሳትን ሱስንዮስና ጸሎተ ንድራን አልቦስምን ዓይነ ወርቅና አስማተ ሰሎሞንን አስጽፎ ይያዝ። የዘመድ ጠላት በፍየል ሥጋ መድኃኒት ያደርግበታል በዘመነ ማርቆስ ረቡዕ ቀን በ፴፯ ዓመቱ በጭንቅ ይታመማል። እስከ ሞት ይደርሳል ወደ ፈጣሪው አጥብቆ የለመነ ያዘነ የተከዘ እንደሆነ ግን ዘመኑ ፷፱ ይሆናል። ፀር ኮከቦቹ ሐመል ደለዊ ዐሰድ ናቸው ግጥሙ ቀውስ ሑት ገውዝ። ማእከላይ ሚዛን ጀዲ ሠውር ናቸው።

 

      ክረምት ይሆነዋል የሰው ገንዘብ ይገባለታል ጥቁር ነገር አይወድለትም ግጥሙ ቀይ ነገር ነው እጀ ሰብአ ይፃረረዋል ከዛሮች ብር አለንጋ ከውላጅ መቅረጭ ዋስ አጋች ይመለከቱታል ከአውሬና ከቁስል የተነሣ ያስፈራዋል ክፍለ ጭዳው ቡሃ በግ ቀይ በግ ነው።

 

      ዓርብና ሮብ አይሆኑትም ሰኞ ማክሰኞና ሐሙስ ቅዳሜ ግጥሙ ነው። የሚሆነው ፈረስ ዳማ ሶቈ ቃጫ ቦራ ነው።

 

       ሰንቡላ መሬት ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደሆነ።

 

      ዓይነ ዘማ ቅንዝረኛ ለሁሉ እሺ ባይ ወራዳ እግረ ቀጭን ትኩሳታም ትሆናለች ትካዜ ይገባታል ዓለማዊ በካና ናት አይሞላላትም መላሷ ተናጋሪ አፈደረቅ ዓቅሟ ደካማ ቀናተኛ ናት። ህመም አያጣትም ነገር ግን አይበረታባትም ዓይነ ጥላ ገርጋሪያት አለባት በቀይ በግ ብራና አልቦ ስምን አጽፋ ትያዝ ጥቁር ፍየል አሳርዳ ደሙን ቀድታ ከባሕር ዳር ይዛ ሒዳ ትጣጠብበት ትንሽ ቆየት ብላ በውሃው ትለቅለቅ መብል መጠጥ ትሰጣለች ገንዘብ አትሰጥም ትነፍጋለች ዓይንና ጥርስዋ መልከ መልካም ናት ወንድ መኰንን ይወዳታል ቃለ ልስልስ ናት ሆዷን ጐኗን ያማታል ሥጋ ስትበላ የሰው ዓይን ያስፈራታል ትጠንቀቅ።

 

                  ፯ኛ ኮከብ ሚዛን ነፋስ።

 

      ይህ ኮከብ ጥቅምት ፯ ቀን በመንፈቀ ሌሊት በዐዜብ በኩል ይወጣል። በተኩላ ይመሰላል ሚዛን ነፋስ እህልና ገለባየ ሚለይ የቀትር ነፋስ ማለት ነው። አጉረምራሚ እንደ ነብር ነጭናጫና ነጣቂ ነው።

 

      ይህ ኮከብ የአለው ሰው ሰውነቱ ቁጡ መላሰኛ ጠላቱ ብዙ ሃይማኖቱ ብርቱ ነው ኑሮው በኀዘን ነው መላና ምክር ዓዋቂ ነገር ተርጓሚ የሰው ልብ ገማች ትምህርት መርማሪ ምሥጢር ዓዋቂ ነው ሙግት ዕድሉ ነው ጠላቶቹ ይፈራሉ ይደነቃሉ ይሸበራሉ ግርማ ሞገስ አለው በድንገት መልስ ለመስጠት ዕድለኛ ነው በሰው ሐሳብ ይመራል በግምባሩ ምልክት አለው ኮከቡ ዘዋሪ ነው አያርፍም ዘመዱን ይጠላል ባዕድ ይወዳል አእምሮው ብሩህ ነው መጭው ነገር ይገለጽለታል ቤተ መንግሥት ክፍሉ ነው ሹመትና ንግድ ክፍሉ ነው ንዳድና የኮሶ ምች ያስፈራዋል ልቡ ብሩህ ጭምት ነው የተማረውን አይረሳም።

 

      ለሰው ቅን በቃሉ ደስ የሚአሰኝ ይመስላል ለመብል እሱር ንፉግ ነው ብዙ ገንዘብ ያገኛል አይሰጥም ለልጁም ቢሆን ከቶ አይሰጥም ገንዘቡ ለባዕድ ይሆናል በእጁ በረከት የለውም አምልኮኛና መሐላ ፈሪ ነው ድሃ አይወድም ከትልቅ ሰው ጋር ሳቅ ጨዋታ ያበዛል ተቀያሚ ኩርፍተኛ በፍርድ አድላዊ ሰው አቃላይ ነው። የተመሰገነ ታሪክ ይኖረዋል አገር ለአገር በመዞር ሀብት ይሆንለታል ገንዘቡ በዕድሜው እኩሌታ ያልቃል።

 

      የድውይ መፈወስ ስጦታ በእጁ አለው። አይታወቅበትም እንጂ ምቀኛና ሐሜተኛ ነው በመብል ጊዜ ጉምጁና ሆዳም ነው የጆሮ ቁስል ያስፈራዋል በዓይኑ ዘማዊ ነው አውስቦ ይወዳል ቀይ ሴት አግብቶ ፯ ልጆች ይወልዳል። ትልልቅ የሆነ ነገር ያስባል ከፍጻሜ ግን አይደርስለትም። ለዛ ያለው ንግግርና ደስ የሚአሰኝ ጨዋታ ያውቃል። ስሙን ለማጥፋት ብዙ ጠላቶች ይነሡበታል ነገር ግን በተንኰላቸው ዝናውንና ዕውቀቱን ስሙንና ታሪኩን እጅግ ከፍ ያለ ያደርጉታል። በድንገተኛ ነገር ድንጉጥና ፈሪ ነው እስራት ያገኘዋል ቤቱ ይወረሳል ይበዘበዛል በዓርብ ቀን ትልቅ አደጋ ያገኘዋል ስለ ሰው መሥዋዕት ሁኖ ሊያልፍ ይወዳል ንግድ ከብት ርቢ እርሻ ክፍሉ ነው። ከ፶ ዓመት በኋላ ባለ ጸጋነቱ እንደገና ይመለስለታል ፍጻሜው በትዳሩ እንደአማረለት ያልፋል። በግራ እግሩና እጁ ምልክት አለበት ቁስል ይገንበታል የግራ አካላቱን ያመዋል በዓይኑና በልቡ ዘር አይቶታልና ዓይኑ ይፈዛል። ከጥቁር ሴት ቂጥኝ ያስፈራዋል በጥቁር ሰው የተነሣ አምባጓሮ ያስፈራዋል በዚሁ ምክንያት ከደንቃራ ይገባና ይታመማል ድርጎ የሚባል ዛር ከሰው ተጋብቶበታል ጽኑ በሽታውም የራስ ምታት ነው የሚብሰውም እሑድ ቀን ነው በዘመነ ሉቃስ የደብረ ታቦት ዕለት ያስፈራዋል። በ፴ ዘመኑ በጦርነት ይቈስላል ራሱን ቀይ ሰው ቢያግመው ይሻለዋል።

 

      ለዚህ መድኃኒቱ የሰው ሰለባ አዝሙድ የጥቁር ውሻ ኩስ ፯ ቀን ቢታጠን ይድናል በ፵ ዓመቱ በቀኝ እግሩ እንደ ቁርጥማት ያመዋል ለዚህ መድሃኒቱ በነጭ ፍየል ብራና ኤኮስንና አካስን ጌርጌሴኖንና አልቦ ስምን አስጽፎ የሸላ ሥጋ ጨምሮ ይያዝ በጥቁር ገብስማ ወይም በነጭ ዶሮ ጭዳ ብሎ ሥጋውን በሰሊጥ አሰርቶ ይብላ በኀዘን ምክንያት ሕመም ያገኘዋል የሰባ ሥጋ ሲበላ የሰው ዓይንና የዛር ውላጅ ያየዋል ወገቡን ጐኑን ሆዱን መላ አካላቱን እየከፈለ ያመዋል ይህ ሕመም ያስፈራዋል ይጠንቀቅ እኩይ ወርኁ መጋቢት ሰኔ ነሐሴ ሠናይ ወርኁ ጥቅምትና ሀምሌ ነው። እኩይ ዕለቱ ሮብ ዓርብ እሁድ ሠናይ ዕለቱ ሰኞ ማክሰኞ ሐሙስ ነው።

 

      ጋብቻው ሓመል ጀዲ ናቸው ሸርጣንም ኅብሩ ነው ኮከብ ፀሩ ሑት ሠውር ሰንቡላ አይሆኑትም ቀይና ነጭ ነገር ክፍሉ ነው መርበብተ ሰሎሞንና ኤኮስን አስጽፎ ይያዝ። አጋጣሚው አሰድ ጀዲ ሑት ነው ማእከላይ ክፍሉ ደለዊ አሰድ ናቸው።

 

      ዘመኑ ሉቃስ ወይም በዘመነ ማቴዎስ ነሐሴ እሑድ ቀን የደብረ ታቦት ዕለት በ፷፭ ወይም በ፸ ዘመኑ ይሞታል።

 

      ሚዛን ነፋስ ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደ ሆነ።

 

      በዘመንዋ ሁሉ ታማሚ በሽተኛ ራስ ምታትና የሆድ ሕመም አይለያትም እንደ ሥራይ ሠርቶባታል ሆድዋን እየበላ ያመነምናታል ዘመዶቿ መድኃኒት ያቀምስዋታል። ምቀኛ ይበዛባታል በፊት ገንዘብ ታገኛለች ትከባለች ደግ ልጅ ትወልዳለች የኋላ ኋላ ግን ችግር ያገኛታል የመርገም ደም ይመታታል ብርቱ ዛር ያድርባታል በሽታዋ ወደ ጣዖት ያሰግዳታል በመጨረሻ ዘመንዋ ግን ንስሓ ገብታ ወደ ፈጣሪዋ ትመለሳለች ለንብረትዋ ልባም ናት የራስዋ ጠጉር ረጅም ለስላሳ ነው ዝሙትነት አለባት መብልና መጠጥ ትወዳለች ልጅም የምትወልደው ወደ ኋላ ቆይታ ነው ከጥቁር ሰው ጋር መገናኘት አይሆናትም ክፍልዋ ቀይና ነጭ ነው።

 

      ይህ ኮከብ ህዳር ፰ ቀን ከ፰ ከዋክብት ጋር በመንፈቀ ሌሊት የሚወጣ ነው። አቅራብ ውሃ ግድብ ውሃ ዓዘቅት ማለት ነው በነብርና ዝሆን በጊንጥም ይመሰላል።

     

      ይህ ኮከብ ያለው ሰው ወዳጅና ጠላቱን አስተካክሎ ይወዳል ገራምና ለጋስ ነው ሰጥቶ ሰጥቶ አይመሰገንም ቁጡ አትንኩኝ ባይ ጨካኝ ዘማዊ አባይ ነው ጸሎቱ ይሠምርለታል ከፍተኛ ባሕርይና የተሠወረ ምሥጢር አለው መሠሪ ነው የወጠነውን ነገር ሁሉ ከፍፃሜ ለማድረስ ይሆንለታል ብዙ ጠላቶች ይነሡበጣል ብዙ ትግልና ፈተና ይደርስበታል የጠላቶቹን ተንኰልና ወጥመድ ቈርጦ ይጥላል፤ብርቱ ኃይለኛ ነው የጠላቶቹን መውደቅ ያያል ደስታና ኅዘን መውደቅና መነሣት ሀብትና ድኅነት ይፈራራቁበታል እንደ ነብር ዘወትር ጠርጣሪና ንቁ ቁጥብ ነው እንቅልፍ እስቲከለክለው ድረስ ከፍ ያለ ሃሳብና ምኞት አለው

 

      በ፴ ዓመቱ ዓይኑን ይጋርደዋል በእጁ ነፍስ ያጠፋል ለኵነኔ የተገባ ነው ልቡ ክፉ ቂም ያዥ ተበቃይ ነው ከወደደ በቶሎ አይጣላም ከአልመነኰሰ አይጸድቅም ከ፶ ዓመቱ የመነኰሰ እንደ ሆነ ምሥጢረ እግዚአብሔርን ለማየት ይበቃል ሀብቱ እንደገና ይፈላል 7 ልጆች ይወልዳል ጥቂቶች ይሞቱበታል በጕልማሳነቱ ዘመን እግዚአብሔርን እንኳ አልፈራም ይላል አንደበቱ ደፋር ልቡ ጨካኝ ነው በሐሰት ሰውን ይረታል ትጉህ ጸላይ ነው የአባቱንና የእናቱን ገንዘብ ይወርሳል እጀ እርጥብ ሢሳያም ነው ራት አያጣም ፍጹም ክፍሉ እርሻና የእጅ ሥራ ነው ሌሊት በሓሳቡ ሁሉን ሲያከናውን ያድራል መሬት ሲነጋ ግን የሚጨበጥ ነገር የለውም ምሥጢሩ ለብቻው ነው ለሰው ማታለል መሸንገልና መደለል ዕድሉ ነው በአንደበቱ ደግ ባለንጀራ ይመስላል ነገር ግን ልቡ ከዳተኛና ተንኰለኛ ነው።

 

      ኃይለኛና ኩሩ ነገር ወዳጅ ወረተኛ ሓሰተኛ ዓይነ ደረቅ ነው በተወለደበት አገር አይደላውም በሰው አገር ይሾማል ክፉ ቃል ቢናገርም ይደነቅለታል ስለ ጥቅሙ ሲል ይታገሳል እንጅ ቁጣ የባሕርዩ ነው የሚበልጠውን ሰው ሲያይ ዓይኑ በቅንዓት ደም ይለብሳል ትዳሩ ይሰናከልበታል። አጋጊጦ ሊመሰግን ይፈልጋል ከ፵ ዓመቱ በኋላ ጠባዩ ይለወጣል ንፉግ ቈጣቢ ይሆናል ማንንም አያምንም ጠርጣሪ ሞገደኛና ተከራካሪ ነው። ለሚስቱ ምቹ አይደለም ግምባሩ ገፊ ነው ቤተ ሰዎቹን ይሸኛል ግራ እግሩን ያመዋል ከፈረስ ከገደል ከዛፍ ወድቆ መሰበር ያስፈራዋል አንድ ጊዜ ከትልቅ ፈተና ይገባል ይህን ፈተና ዘልቆ ግን ከትልቅ ደረጃና ማዕረግ ይደርሳል ለዘመዶቹ ረጂና መመኪያ ይሆናል በሽምግልና ዘመኑ ዘመዶቹንና ወገኖቹን ይጠቅማል።

 

      ሌጌዎን የሚባል ጋኔን በፊትና በኋላ ይከተለዋል ከሴት መድኃኒት ይጠንቀቅ ቡዳ ቁስል ቁርጠት ቁርጥማት ያመዋል ሚስቱን በደም ያስፈራታል እጁን እግሩን ራሱን ያመዋል ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ ሲሻገር በመጋቢት ሮብና ዓርብ ቀን የምታት በሽታ ያገኘዋል መድኃኒቱ የዶሮ ኩስ የሚባል ዕፅ ጉመሮ የእርግፍጋፎ የእነዚህን ሥር ፯ የጊንጥ ራስ የምጥማጥ ሥጋ የፍየል ቀንድ ፩ ላይ ቀምሞ ፫ ቀን ይታጠን። ከእነዚሁ መድኀኒቶችም ቀንሶ በአምሳያ ላሚቱ እናትና ልጅ ፩ ጠጉር) ቅቤ ለውሶ ፯ ቀን ገላውን ያባብስ። ግንቦትና ጥቅምት ሕመም ያስደነግጠዋል መድኃኒቱ ጉመሮ ጊዜዋ ምስርች ይታጠን። በጥቁር ፍየል ብራና ሓፁረ መስቀልና ቆጵያኖስን አስጽፎ ጊንጥ ጨምሮ ይያዝ ዓሣና ሰሊጥ አብስሎ ይብላ አጥንቱንም አንቀጸ ብርሃን አስደግሞ ይታጠን። የቀረጥ ተቀጽላ ይያዝ።

 

      በተወለደ በ፪ በ፴፭ በ፵ ዓመቱ ብርቱ ሕመም ያስፈራዋል መድኃኒቱ ጥቁር ዱልዱም ዶሮ ወይም ጥቁር የገብስማ ዶሮ ጭዳ አድርጎ የቅድሙን መድኃኒቶች በዶሮው ደም ነክሮ ከትቦ ቢይዝ ደግ ይሆንለታል።

 

      ሠናይ ወርኁ መስከረም ኅዳር ታህሣስ ጥር ነው እኩይ ወርኁ ጥቅምት የካቲት መጋቢት ሠናይ ዕለቱ ሰኞ ማክሰኞ ሐሙስ። እኩይ ዕለቱ ዓርብ ሮብ ነው። ኮከብ ፀሩ ሓመል ገውዝ ሚዛን ነው። ግጥሙ ደልዊ ሠውር አሰድ። ማእከላይ ቀውስ ሸርጣን ሰንቡላ ናቸው።

 

      በዘመነ ዮሐንስ በጥምቀት ወር እሁድ ቀን በ፸፯ ዓመቱ ይሞታል ያዘነ የተከዘ የጸለየ እንደሆነ ግን እስከ ፹፭ ይቈያል።

 

      አቅራብ ውሃ ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደ ሆነ

 

      ማኅፀንዋ ስፋሕ ነው ቡዙ ልጆች ትወልዳለች ሾላ ላይ ይጸናወታታል ከጋኔን የተቀላቀለ የዛር ውላጅ ይመለከታታል ልጆችም ይሞቱባታል ለጊዜው ቁጡ አኵራፊ ሆደ ባሻ (ገር) ናት ኋላ ግን ቻይ ቶሎ ተመላሽ ናት። ሃብቷንም ፊት አሳይቶ ኋላ ያጥርባታል ጕርሻ ትወዳለች ደረቅ ናት ነገርዋ ለሰው አይጥምም ፊተ ረጅም ናት ቅንዝረኛነት አታጣም። ከክንፉና ከእግሩ ጥቁር የአለበት ነጭ ዶሮ ጭዳ ታድርግ። በጥቁር ፍየል ብራና ሓፁረ መስቀል አጽፋ ትያዝ። ዕድሜዋ ፷፭ ዓመት ነው።

 

                ፱ነኛው ኮከብ ቀውስ እሳት

 

      ይህ ኮከብ ከ፰ ከዋክብት ጋር በታህሣሥ ፲፩ ቀን በዕርበት ፀሓይ የሚወጣ ነው። ቀውስ እሳት ረመጥ ወይም የተዳፈነ እሳት ይባላል። በጅብና በአውራሪስ ይመሰላል።

 

      ይህ ኮከብ ያለው ሰው ደስታውንና ሓዘኑን ጥቅሙንና ጉዳቱን ለሰው አይነግርም ምሥጢሩ ሁሉ ሥውር ኃይሉ ድብቅ ጻድቅ መንፈሳዊ እግዚአብሔርን ፈሪ ጾምና ጸሎቱ ሥሙር ነው። ብቸኝነትን ይወዳል ልቡ ቅን ነው ምሽቱ ትሞትበታለች ወይም ትፈታዋለች ገርና ቅን ሰው አማኝ ነው በገርነቱ ትዳሩን ያሰናክላል። ሓሳብ ያበዛል አይፈጸምለትም ነገር ይረዝምበታል ቶሎ አይቆረጥለትም ቁም ነገራምና ትንቢተኛ ይሆናል አስቀድሞ እንደሚያሸንፍ ሳይገምት በቶሎ ለጠብ አይነሣም በሰው ነገር ዘሎ አይገባም ገርነት አለው  ራሱን አኩሪ ተመካሒ ብልሕ ጥበብ አዘጋጅ ለሴት ገራምና የዋህ ነው በትንሽ ነገር አዝኖ በትንሽ ነገር ይደሰታል። ጥፋትና ስሕተት ሞልቶታል።

 

      አይነሣም እንጂ ከተነሳ እንኳን ሰውንና ፈጣሪውንም ይደፍራል ከያዘ አይለቅም ዓይኖቹ ልሞች ናቸው ድምጹ ለሰው ደስ የሚያሰኝ ነው በቤተ መንግስት ይኑር ቀይ ነገር ክፍሉ ነው። ከጥቁር ከብት ወድቆ ይሰበራል በዓይኑና በፊቱ ልዩ ምልክት አለበት ብዙ ልጆች ይወልዳል አብዛኛዎቹሴቶች ይሆናሉ ሦስት ዕድል አለው ከሦስቱ ፩ እንኳ ቢይዝ ሃብታም ይሆናል ፩ዱን ከአልያዘ ግን ተራ ሰው ሁኖ ይቀራል።

 

      ሰው ያማዋል ሓሜት ልብሱን ነው ቀጠሮ አፍራሽ ነው በሴቶች ዘንድ ተወዳጅ ነው እድፋም ልብስ አይሆነውም ዘወትር ነጭ ይልበስ ሰው ሁሉ ይፈራዋል ገራም ነው የኋላ ኋላ ምንኵስና ክፍሉ ነው የሽንት ምጥ ያስፈራዋል።

 

      ብዙ ምቀኞች ይነሡበታል ያባርሩታል ሥራውን ያሰናክሉበታል ነገር ግን በማሰናከላቸው ይጠቀምበታል ብርቱ ነኝ ባይ ነው ነገር ግን ወዳጆቹ ዘወትር ያሸንፉታል። ዘመዶቹ አይወዱትም እርሱም ከዘመድ ይልቅ ባዕድን ይጠቅማል ነገር ይቈሰቁሳል የቈሰቈሰው ነገር እስከ ዳር ሳይደርስ አያርፍም ቀይ ነገር ክፍሉ ነው በቀይ ቦታ ይኑር ለጤናውና ለኑሮው በገጠር ይመቸዋል ክፍሉ ግን ከተማ ነው። በምሥራቅ በኩል ይኑር።

 

      ንዳድ ያስፈራዋል ዓይኑና ጥርሱን እንደቁርጥማት ያመዋል እንጀራው በሽበት ነው ነጭና ቀይ በግ ዳለቻ ፍየል ይረድ የዐማኑኤልን ጠበል ይጠጣ በ፪ ወይም በ፲፪ ዓመቱ የምጥማጥ የሸላ የፍልፈል ሥጋ ሥረ ብዙ ዳብዛ ጽጌረዳ ሥራቸውን ከእነዚያ ሥጋዎች ጋር ፩ነት ደቁሶ ይታጠን።

 

      በማቴዎስ እሥራት ያስፈራዋል በመስከረምና ታኅሣሥ የካቲት ነሐሴ ዓርብ ሮብ ይጠንቀቅ ክፉ ነገር ያገኘዋል መብረቅ ያስፈራዋል። በዘመነ ዮሐንስ ቅዳሜ ቀን ይሾማል በ፵ ዓመቱ መቅሠፍትና የሰው ልሳን ጭምር ያስፈራዋል። ነገር ባሰበ ጊዜ ልቡ ይዘራል በእግሩና በእጁ ምልክት አለበት በዘመነ ማቴዎስ ሰኔ ፲፪ ቀን ዕንቅፋት ያገኘዋል ጥቁር ፍየል ይረድ ዓሣ በሰሊጥ አሠርቶ ይብላ በታመመ ጊዜ ነጭ ዕጣን ሎሚ የዓሣና የከርከሮ ሥጋ ቀቅሎ ይብላ መረቁንም ይጠጣ።

 

      በተቆጣ ጊዜ ጀርባውን ያመዋል ሐሳብ ያበዛል ነቀርሳ ያስፈራዋል መድኃኒቱ የአሜራ ሥር የዋንዛ ሥርና ቅርፊት አሣርሮ በቅቤ ለውሶ ከሚያመው ላይ ያድርግ። በሰኔ ወር እንደ ሳል ያመዋል ያሮክ የሚባል አስማት ኤኮስን ጨምሮ በነጭ ዶሮ ፊኛ ጽፎ ይያዝ።

     

      እጁን ቁርጥማት ያመዋል ዓይነ ጥላው በነጭ ፍየል ወይም በነጭ በግ ብራና አልቦ ስምና ፬ቱን ኤኮሳትን ሱስንዮስንና ጸሎተ ንድራን አስጽፎ ከነዚያ ከተጻፉት ሥሮችና ሥጋዎች ቀምሞ ከዓይነ ጥላው ጋር ይያዝ።

 

      የሚመለከቱት ዛሮች ቆስጤ ጅጀኖ ከውላጅም ኩርንችትና በጣሳ ናቸው። በቀኝና በግራው እየተዘዋወሩ ያበሳጩታል ሴት ዛር ታድርበታለች ዓይኑን ትተናኮለዋለች ደም አስመስላ ታፈዝበታለች እግሩን ራሱን ጫንቃውን ልቡን ያመዋል ጆሮውንም ያደነግዘዋል ለዚህ ሁሉ አስቀድሞ የተጻፈውን መድኃኒትና ዓይነ ጥላውን ቢይዝ ይሻለዋል። ጭዳው ዳለቻ ፍየል በግ ዶሮ ነው። ክፍለ ፈረሱ ቡላ ሐመር አፈሾሌ ቡላ በቅሎም ይጫን።

 

      እኩይ ዕለቱ ሐሙስና ቅዳሜ ነው ሠናይ ዕለቱ ረቡዕና ዓርብ እሑድ ነው። በዘመነ ማቴዎስ የሰኔ ተክለ ሃይማኖት ዕለት ያስፈራዋል። ጋብቻው ሑት ሰንቡላ ገውዝ ፀሩ ሸርጣን ሠውር አቅራብ ነው። ማእከላይ ጀዲ ሐመል ሚዛን ናቸው። በዘመነ ማቴዎስ በ፹፰ ዓመቱ ቅዳሜ ቀን ይሞታል።

 

       ቀውስ እሳት ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደሆነ

 

      ላህይዋ መልካም ነው ደም ግባት አላት ሳቂተኛ ትሆናለች ዓይነ ዘማ ናት ሆዷ ቂመኛ ነው ግን በቶሎ ትመለሳለች የሰውን ባሕርይ መጣኝ ልበ ብልህ ናት ልክ ዐዋቂ ቤቷን ወዳጅ ወዳጅዋን አፍቃሪ ቁም ነገራም ናት ደጋግ ልጆች ትወልዳለች ሆዷን ልቧን ዓይኗን ያማታል በወሊድ ደም ያገኛታል የርግብ ሥጋ በሰሊጥ አዘውትራ ትብላ። በደም ግባቷ ትመካለች ጥርሰ መልካም ናት ማን ይበልጠኛል ትላለች። ዕድሜዋ ፷ ዘመን ነው።

 

                     ፲ኛው ኮከብ ጀዲ መሬት

 

      ይህ ኮከብ በሐምሌ ወራት በምሥራቅ በኩል በመንፈቀ ሌሊት ይወጣል። ኮከብ ጀዲ በንስር ወይም በሸረሪት ይመሰላል ጀዲ መሬት ደባይ (ዋልክ) መሬት ማለት ነው ጀዲ ነገረ ወዲ ይባላል።

     

      ይህ ኮከብ ያለው ሰው እንደ ንስሩ ፈጣሪ ነው ፍርሃት የለውም አደጋ ጣይ ጨካኝ ኩርፍተኛ ባልጀራውን አክባሪ ጨዋታ ወዳጅ ነው ወዲያው ከአልተበቀለ ቂም አይዝም። ጽሕፈት መሰንቆ የጌታ ቤት  እርሻ ክፍሉ ነው በደባይ (በጥቁር) መሬት ይኑር ነጭ ከብት አፈ ጭቃ ፈንዝማ ይረባለታል በሰው ዘንድ አይለማመጥም ዝምተኛ ነው ብቸኝነት ይወዳል ራሱን ማዋረድ አይወድም ግን ሰው ይወደዋል ለሰው ከቶ አድልዎ የለውም ቀጥ ያለ ሐቀኛና እሙን ነው ትንሽ እልክ አለበት በእልኩ ከትልቅ አደጋ ይደርሳል ክፍሉ ጠይም ሰው ነው ስንደዶ ከሚበቅልበት ቦታ ይኑር ልቡ ብሩህ እግዚአብሔርን ፈሪ ሕልሙ የታመነ ነው ከፍ ያለ ማሰብ አለው ስጦታው ነውና የእጅ ሥራው ይደነቃል በምቀኞች ብዙ ጊዜ ይንገላታል ይቀኑበታል ይመክሩበታል በመጨረሻ ግን ያሸንፋል አትክልትና እርሻ በጥቁር መሬት ይሆንለታል ተጸጻች ምሕረተኛ ቸር ይቅር ባይ ነው ምቀኛና ሌባ አንድ ጊዜ  ንብረቱን ይዘርፉታል በልቡ ትዕቢት ያበዛል እስከ ዘመነ ሽምግልናው ድረስ እጅግ ዘማዊና ቅንዝረኛ ነው በሴት ነገር ተከሶ በፍርድ ቤት ይቆማል። በሴት ነገር የተነሣ በእጁ ነፍስ ያጠፋል በብርቱ እልከኛ ነው አዛኝም ነው የኋላ ኋላ ወደ አባቱ እርስት ይመለሳል። ጥቁር ነገር ሁሉ ክፍሉ ነው። በሽምግልና ዘመኑ መጠጥ ያበዛ እንደሆነ ዓይኑ ይጠፋል ጤናው ይሰናከላል የራሱ ጠጉር ሽልት ነው በቀኝ እጁ ምልክት አለበት ሀብታም ነው መኳንንት ይወዱታል።

 

      ሳይደኸይና ሳይበለጽግ በልክ ሆኖ ደስታና ኃዘን እየተፈራረቀበት ይኖራል ጸሎቱ ግን ሥሙርና የተወደደ አስብ ያለው ነው። ስደት ያገኘዋል ዕድሉ ነውና በሰው አገር ይከብራል በመመላለስ ሀብት ያገኛል የመልዕክት ጉዳይ ይከናወንለታል ባሕርዩ እጅግ ንጹሕና የዋህ ነው ገንዘብ ይወዳል ንፉግ ግን አይደለም መቆጠብን ያውቃል ዓለማዊነትን ይወዳል እስከ ሽምግልና ዘመኑ ድረስ ዘማዊነት አያጣውም እጅግ ቅንዝረኛ ነው መጻሕፍት ለመጻፍ ቅኔ ለማስተካከል ስጦታ አለው የተማረ እንደሆነ ማንበብና መተርጐም ጽሕፈትም ክፍሉ ነው እሳት ይለክፈዋል ውሃ ሙላትና መብረቅ ያስፈራዋል። ዓይኑ እንደ መነጽር ነው ልቡ ብሩህ የክርስቲያን ወዳጅ የአረመኔ ጠላት ነው ቂጥን ንዳድ ውጋትና ኩፍኝ ያስፈራዋል ሌሊት በዝናም ወደደጅ አይውጣ በ፳፪ ዓመቱ ይታመማል በ፶ ዓመቱ ሞት ያስፈራዋል።

 

      የመጀመሪያ ሚስቱ ትፈታዋለች ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ በደህና ይኖራሉ ቤተ ሰዎቹና ጐረቤቶቹ ይመቀኙበታል እግር ብረት ያስፈራዋል በብረት ቁስል ያስፈራዋል ፀሓይ ሳይወጣ መጓዝ አይመቸውም ዘፈንና ዜማ ይወዳል ቁም ነገራም ነው ሐሰት አይወድም ቀይ ሴት ዘመዱ በጉሽ ጠላ ወይም በስንዴ እንጀራ በዘመነ ማቴዎስ በግንቦት ወር መድኃኒት ታደርግበታለች። በጀርባውና በጭኑ ምልክት አለበት አንድ ጊዜ እግሩን ብርቱ ቁስል ያመዋል።

 

      መጋኛ ቀኝ እግሩን ጉልበቱን ወገቡን ያመዋል ሆዱን ይነፋዋል የዛር ውላጅ ያስፈራዋል የሰው ዓይን ይወጋዋል የሚመለከቱት ዛሮች ብር አልንጋ ሰይፍ ጨንገር ዕንቁላል ናቸው። ዋስ አጋች የሚባል ዛርም ገና ሲወለድ በደም ላይ ጀምሮ ቁራኛ ሆኖ ይጠባበቀዋል ጠቋርም ይወጋዋል ሁለመናውን ይልሰዋል። በጥቁር ፍየል ብራና መርበብተ ሰሎሞንንና መስጥመ አጋንንትን መፍትሔ ሥራይንም አጽፎ ይያዝ። ዳለቻ ወይም ጥቁር የጥቁር ገብስማ ዶሮ ወይም ነጭ ዶሮ ጭዳ ብሎ ይረድ።

 

      ምን ጊዜም ሲያመው ለሕመሙ የሚበጀው ቡይት ወፍ ዓሣ ሰሊጥ አፍርንጅ በጥቁር ላም ወተት እያማገ ይብላ። የበቀለ ቀንድ የቁልቋል ሥር ዘምባባ ሥር አንድ ላይ ደቁሶ በመሃል ራሱ በጥቶ ያግባ። የቡያ የርግብ ሥጋ  የሪያ ሥጋ የአውራሪስ ቀንድ አንድ ላይ አድርጎ ይታጠን። ኤፍራን ቀለም ነጭ ዕጣን አበሱዳ በጠጅ አንፍሮ ይጠጣ።

 

      ከከዋክብት ግጥሙ ሐመል ሚዛን ሸርጣን ናቸው። ፀሩ ቀውስ ገውዥ አሰድ ነው። ማእከላይ ደለዊ ከወሮችም የካቲትና መጋቢት ግንቦት አይሆነውም ኅዳርና ታኅሣሥ ግጥሙ ነው። ሮብና ዓርብ ቀን አይሆነውም ሰኞና ቅዳሜ ግጥሙ ነው። በዘመነ ማርቆስ በግንቦት ፲፫ እሑድ ቀን በ፸ ዓመቱ ይሞታል ቢጸልይ ቢያዝን ቢያሳዝን ፹ ይሞላዋል።

 

       ጀዲ መሬት ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደ ሆነ

 

      በጥርስዋ ላይ ምልክት አለባት ሃብታም ናት ጥሪትና ራት አላት ልጆች ትወልዳለች ፩ ልጅ ይሞትባታል ደግነትና ቸርነት አላት የዋህነት አለባት ሰውነቷን ችላ ትለዋለች ሰውን አማኝ ናት ግን ወዳጆችዋ ይከዷታል ንፉግ ናት የኋላ ኋላ ትቸገራለች አረመኔ ባዳ ያገባታል። በወሊድ ደም ያስፈራታል የደም አብነት ትያዝ በጥቁር ፍየል ብራና አስማተ ሰሎሞንን ከእሪያ ሥጋ ጋር አስጽፋ ትያዝ በ፵ና በ፶ ዓመትዋ ሞት ያስፈራታልና ትጠንቀቅ።

     

      የሚመለከቷት ዛሮች ቁርጠትና ሚሚት ናቸው በአንገቷ ኮልባና መዳብ ቀለበት ብታሥር ይሻላታል ቡሃ በግ ጭዳ ብላ አሳርዳ በደሙና በፈርሱ ትታጠብ።

 

                     ፲፩ኛው ኮከብ ደለዊ ነፋስ።

 

      ይህ ኮከብ በጥር ፲፪ ቀን ከደቡብ ይወጣል በበሬ ይመሰላል ደለዊ ማለት ሁሉን አደላዳይ ወይም ኃይለኛ ማለት ነው በጐሽ በአንበሳም ይመሰላል።

 

      ይህ ኮከብ ያለው ሰው ብርቱ ኃይለኛ ጠብ ወዳጅ ትምክሕተኛ ነው ያሰበውን ካላደረገ አይመለስም ትጉ ሠራተኛ ፍጥረት ነው ለኑሮው በፊቱ ላብ (ወዝ) ይታገላል ሥራም ይወዳል ብርቱ ደም ካፍንጫው ይነስረዋል ሣቅ ያበዛል አንገቱን አቀርቅሮ ይሄዳል በገንዘቡ የተነሣ ይቈጣል የፊቱ አወራረድና የግንባሩ አኮመታተር በሬ ይመስላል ደም ግባታምና ተወዳጅ ግርማ ያለው መልክ አለው እርሻ ክፍሉ ነው ንብና በግ ይረባለታል ነጭ ነገር ይሆነዋል ጫወታ ዐዋቂ ነው መለማመጥን አይወድም እንጂ መኳንንት ያፈቅሩታል። ጌታ ይሆናል ገንዘቡ ለልጁ አይተርፍም ዕንቅፋታም ነው በ፲፭ በ፴ በ፵ ዓመቱ ይጠንቀቅ የልብ ሕመምና ሳል ያስፈራዋል ቀይ አረመኔ በግራ እጅዋ ምልክት የአለባት ሴት ቢያገባ ይወልዳል ትሆነዋለች የአባቱን እርስት ይወርሳል ብዙ ልጆች ይወልዳል ዘማዊነት አለው እስከ ዘመዶቹ ማውሰብ ይደርሳል።

 

            መልከ ቅን ተወዳጅ ነው ዘመኑን ሁሉ በሰላምና በደስታ ይኖራል ከሴት ፍቅር የተነሣ ከትልቅ አምባጓሮ ይደርሳል ሁሉ ጊዜ መጠንቀቅ የሚገባው ከደም ንስርና ከውጋት ሕመም ነው ደለዊ ነፋስ የመሬት ሠራተኛ ብቻ አይደለም የጥብቅነትና የንግድም ሥር ዕድሉ ነው ነገር ግን በሰው ዘንድ ስሙ በክፉ ይነሣል። ፍርድና ርትዕ ምርመራም ያውቃል ንግግሩና አንደበቱ ተወዳጅ ነው መተቸትና ማስረዳት መተርጐምም ያውቃል ጠባዩ ብርቱ ነው ሐሰትም ቢሆን በተናገረው ይጸናል ጥልቅና ሩቅ የሆኖ ምሥጢር ያውቃል እግዚአብሔርን ይፈራል የጉራና የመግደርደር ባሕርይ አለው ወረተኛ ነው ገንዘብ ያባክናል ያገኛል ያጣል ሃብታም ነው ብዙ መከራ አያገኘውም ከመከራና ከፈተና ለመውጣት ብልሕነት ተሰጥቶታል ወዳጅና ጠላት ባዕድና ዘመድ አይለይም ቂም የለውም እንደ ርግብ የዋህ ነው አይሆንለትም እንጂ ንጹሕና ጌጸኛ ልብስ ይወዳል እድፋም ልብስ አይሆነውም የባዕድ አገር ዕድሉ ነው ባለ ጸጋ ይሆናል በተወለደበት አገር ግን ጠላት ይበዛበታል ሰጥቶ አይመሰገንም ለአጭር ጊዜ በድኅነት ላይ ይወድቃል ተበድሮም ቢሆን ሰውን መምሰል ይወዳል የሰው ምክር አይሰማም በአደጋና በጭንቅ ጊዜ ይሸበራል አይችልም ይጃጃል ወላዋይ ነው ሳያስበው በአጋጣሚ ብዙ ገንዘብ ያገኛል። በሐሰት ይምላል ነገር ይጠብቃል እኔ ያልሁት ይሁን ይላል ሰውን ይንቃል ያቃልላል በምሥራቅ አገር ክፍል አለው የኮሶ ምች ያስፈራዋል።

 

      በዘመነ ማርቆስ በጥቅምት ወር ያመዋል መድኃኒቱ ቀይ ወይም ነጭ ዳለቻ በግ ገብስማ ዶሮ ይረድ እውነተኛ ነው ዋስ መሆን አያምርበትም በትንሽ ነገር ንጉሥ የሆነ ያህል ይደሰታል። ደለዊ ከዘመዱ ጋር አይኖርም

እርሱም ዘመዱን አይወድም መቃብሩንና ሬሳውን እንኳን ሊያይ አይፈቅድም። የሚመለከተው ዛር ብር አለንጋ ነው የእግሩን ጫማ ጫንቃውንና ጉልበቱን ያመዋል ከደጁ ስራይ ይጣልበታል አስቀድሞ ለዚህ የሚሻለው የቀይ ከላድማ ፍየል ቀይና ገብስማ ዶሮ ይረድ ቀይ ወይም ነጭ የአዳል በግ አርዶ መረቁን ይጠጣው በብራናውም ትምህርተ ኅብአትንና ስመ አምላክን ኤኮስንና አካስን አጽፎ ይያዝ ዓሣና ሰሊጥ ወገርትና ምስርች ጠምበለልም ሥራቸውን ሰናፍጭም ቅጠሉንና ፍሬውን እነዚህን ሁሉ በ፩ነት አሰርቶ መረቃቸውን ይጠጣ።

 

      ሆዱን ያመዋል በማርቆስና በሉቃስ ዘመን በጥቅምት ወር ዓርብ ቀን ያስፈራዋል ተጻራሪዎቹና ለሞት የሚያደርሱት ሰይፍ ጨንገር ወሰን ገፊ ጠቋር ዲራ ጉቾች ናቸው መድኃኒቱ ከላይ የተጻፈው ነው።

 

      ፀር ኮከቦቹ ሸርጣን ሰንቡላ ጀዲ ናቸው። የክፍል ኮከቦቹ ደግሞ አሰድ ሠውር አቅራብ ማዕከላዊ ሑት ገውዝ ቀውስ ናቸው። ከዘመን ሉቃስ ከወር የካቲትና ጥቅምት አይሆነውም። መልካም ቀኖቹ ሰኞና ሐሙስ ነው። ክፉ ቀኖቹም ሮብና ዓርብ ናቸው።

 

      የዕድሜው ልክ ፷፭ ዓመት ነው ቢያዝን ቢጸልይ ቢያሳዝን ፸፭ ይሞላዋል። በዘመነ ሉቃስ ነሐሴ ፲፫ ቀን የደብረ ታቦር ዕለት ይሞታል።

 

       ደለዊ ነፋስ ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደሆነ

 

      እግርዋ ቀጭን መልከ ደማም ትሆናለች ቁም ነገረኛ ወላድ ሃብታም ባለ ብዙ ፍሬ ትሆናለች የሰው ፍቅር አላት ነገር ግን ትንሽ ቀን ትቀነዝራለች በወሊድ ጊዜ ደም ያስፈራታል ዕጣንና ከርቤ ትታጠን። እጅዋ ለመስጠት ቸርና ለጋስ ናት የተናገረችውና የአሰበችው ፈቃድዋ ካልሆነ በጅ አትልም ደግ ምክርና የነገር አመላለስ ታውቃለች በነጭ የአዳል በግ ብራና ትምህርተ ኅቡአትንና ኤኮሳትን አስጽፋ ትያዝ ደጋግ ልጆች ትወልዳለች በቤት አያያዝ ታውቅበታለች ቁጠባና ብልሕነት ዕድልዋ ነው። ዕድሜዋ ከ፶፭ና ከ፷ አያልፍም።

 

                 ፲፪ኛው ኮከብ ሑት ውሃ።

 

      ይህ ኮከብ ከ፲፪ ከዋክብት ጋር በየካቲት ፲፪ ቀን በምሥራቅ በኩል የሚወጣ ነው። ምሳሌው ከይሲ ነው በዓሣና በአንበሳም ይመሰላል ሑት ነገር ኰትኩት ይባላል።

 

      ይህ ኮከብ ያለው ሰው ነገሩ ሁሉ ጠንካራና ጥብቅ ነው ቁጡና ደፋር ነው በተቈጣ ጊዜ ልሳኑ ይታሰራል ሰጭና ለጋስ ነው ለድኃ ይራራል ጾመኛና ጸሎተኛ እግዚአብሔርን ፈሪ ቤተ ክርስቲያን አዘውታሪ ይሆናል። ከእናቱ ማኅፀን የተመረጠ አስተዋይና ብልሕ ነው ተንኮለኛና ቀናተኛ መሠሪና ምቀኛ ነው ይህን ሁሉ ግን በሽንገላ (በፖለቲካዊ) ተግባሩ ሠውሮት ይኖራል ትሑትና ሰው አክባሪ መስሎ ይታያል ዓቅም ሲያንሰው እንደ እባብ ብልሕ ነው ሲመቸው ግን የዋህነት አይሆንለትም ጨቅጫቃ ነው ነገር በቶሎ አይቈርጥም ከልክ ያለፈ ዘማዊ ነው አይታወቅበትም እንጂ እስከ ዘመዱ እንኳ ያወስባል መላ ዓዋቂ ከዓቅሙ በላይ ኩሩ ነው እንኳን ሰውን እንሰሳና አውሬም ቢሆን ለማታለልና ለማዳ ለማድረግ ዕድለኛ ነው። አገረ ገዥ ይሆናል። ሥርዓት ያውቃል። እግሩ ጠማማ ምሕረት የሌለው ተበቃይና ጨካኝ ነው ጸጉሩ ልስልስ ድምጹ ቃና ያለው ነው በሽምግልና ወደ ፈጣሪው ይመለሳል በገዳምና በምንኩስና ቢኖር  ክፍሉ ነው ኃጢአቱ ይሰረይለታል። ነቢያትና ሐዋርያት ባረፉበት ቀን ያርፋል። ገንዘብ ቢኖረውና ባይኖረውም ሁሉም ፩ ነው ልጆች ይወልዳል ንግድና መልእክት ይስማማዋል ተስቦና ተቅማጥ ያስፈራዋል። በቤቱ አይሞትም ድንገተኛ ነው።

 

      ነገሩ ሁሉ ጥብቅና እሙን ነው ገንዘብ ያበደረው ሰው ተመልሶ ጠላት ይሆነዋል ሲሔድ ፈጣን ነው የሚሮጥ ይመስላል እንግዳ ማስተናገድ ይወዳል ማናቸውም ምሥጢር አይሠወርበትም ጨዋታና ቀልድ ያውቃል ይወዳል ከ፶ ዓመቱ በኋላ ገንዘቡ ያልቅበታል ቅንዝረኛና ዘማዊ ነው በትምህርት እጅግ አይሰለጥንም ዓዋቂና አስተዋይ ነው ተኝቶ ሐሳብ ያበዛል ብዙ ጊዜ ገንዘቡ ይሰረቅበታል ወይም ይወረሳል ማታ ተጣልቶ ማለዳ ይታረቃል ጠባዩን ማንም አያውቀውም ተለዋዋጭና ሥውር ነው።

 

      በልግስናው ዝናው የታወቀ ነው እርሻና ንግድ ይሆንለታል አህያና ንብ ይረባለታል ዳተኛና ሰው ተጫኝ አያሳዝንና አያስደስት ነው ዘመዱና ጐረቤቱ ይጠላዋል ቢያበላና ቢያጠጣ አይመሰገንም ዘመዱን ይንቃል ያልታሰበ ጸጋ ያገኛል ጊዜ ካነሣው ጋር ይፋቀራል ያውም ለጥቅሙ ሲል ነው ከሁሉ ሰው ጋር ፈገግተኛ ነው ውስጣዊ ባሕርዩን አይገልጽም እስከ ባሕር ቢነግድ ክፍሉ ነው መጠጥ ይወዳል ጥቁር ከብት ዕድሉ ነው በምሽቱ ምክንያት ነገር ያገኘዋል በልጅነቱ ገንዘብ ያገኛል በመካከል ያጣል እንጀራው በሽበት ነው።

 

      በእጁ በእግሩ በወገቡ ምልክት አለበት ሆዱን ይነፋዋል ብረት ያቈስለዋል ከንዳድና አውሬ ከማደን ይጠንቀቅ በሁሉም ነገር ረዳቱ ፈጣሪው ብቻ ነው እንጂ ሰው ሁሉ ጥፋቱን ይጠብቃል የሴት ሥራይ ያስፈራዋል የጥቁር ገበሎ ሥጋ ፩ በቀል። ፍየለ ፈጅ እዩባን የምድር እምቧይ በ፩ነት አድርጎ በጥቁር ፍየል ብራና አስማተ ሰሎሞንና ባርቶስን አስጽፎ ይያዝ። ዓርብ ሮብ እሑድ ክፍሉ አይደለም እንቅፋት ያገኘዋል መድኃኔ ዓለምን ያክብር ደረቅ ተሟጋች በእልኩ ዘላቂ ነው በደጋ አገር ይቀመጥ።

 

      በተወለደ በ፵ ዓመቱ ሁለመናውን ብርቱ ቁስል ያስፈራዋል ወጣሌ የሚባል የደጋ ዛር በመንፈቀ ሌሊት ወደ ደጅ ሲወጣ ተጠናውቶ ይይዘዋል ብራቅ ወንዝ አድርቅ መዓት ወረድ ኩርንችት የሚባሉ ዛሮች ይይዙታል ሌሊት በሕልሙ በድቀተ ሥጋ እየመጡ ያስደነግጡታል ዋስ አጋችና አጋም ጣስ ዕንቁላልና ማኅደር ይጫወቱበታል ከውሃ ጥም የተነሣ ብርቱ ሕመም ያገኘዋል ራሱን ወገቡን ዓይኑን ይነድለዋል ዘመዶቹ መድኃኒት ያደርጉበታል በሆዱ እንደ ሥራይ ይሠራበታል እያስጮኸና እያፋሸገ ያመዋል።

 

      ለዚህ በሽታ መድኃኒቱ ዝንጅብልና ኮረሪማ ሰሊጥና ቁንዶ በርበሬ እሩህና ከናንህ በአሞሌ ጨው አጣፍጦ ወንጌለ ማርቆስና ኪዳን ደግሞ በዓሣ መረቅና በቀይ ጤፍ እንጀራ ፈትፍቶ ፯ ቀን ይብላ። በሐምሌ ወር መንገድ አይሒድ አይሆንለትም።

 

      እኩይ ወርኁ ጥቅምት ግንቦት ነሐሴ ሠናይ ወርኁ መስከረምና ታኅሣሥ ነው። ኮከብ ጸሩ አሰድ ሚዛን ደለዌ ክፍሉ ገውዝ ሰንቡላ ቀውስ ናቸው። በተወለደ በ፹፰ ዓመቱ በዘመነ ዮሐንስ በሐምሌ ወይም በመጋቢት ዓርብ ቀን ይሞታል።

 

      ሑት ውሃ ኮከብ ያላት ሴት የሆነች እንደ ሆነ።

 

      መልከ ቀና የማታሳልፍ ቀናተኛ ናት ባሏንም ታስቀናዋለች ከወዳጁ ጋር ታጣላዋለች ዘማዊ ናት አውስቦ አትጠግብም ነገር አታቋርጥም ደፋር ምላሰኛ ናት መጠጥ ትወዳለች ስካር ይቃወማታል ችኮ ሸውሻዋ ናት ነገር ታማታለች ንፍገት አለባት ባልትና አታጣም እጀ ሰብእ ያስፈራታል ልጅ ይሞትባታል የመርገም ደምዋ ይፈታባታል የጋላ ዛር ያድርባታል ወደርሱ ያስመልካታል ወጣሌ የሚባል ዛር በወቅት ጊዜ ይመታታል እግሯን ይቈረጥማታል አቅዳፌርና ኤኮስን በዳለቻ በግ ብራና አስጽፋ ትያዝ።

 

@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@@

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ። ንጽሕፍ እንከ ዘንተ መጽሐፈ ዓውደ ነገሥት ዘተረክበ በደሴተ ፃና እምደብረ ደቅአስጢፋ። ዘአስተጋብእዎ ቀደምት አበው ጠቢባን ወፍልሱፋነ ዓለም። ከመ ይኩኖሙ መድኃኒተ ሥጋ ወነፍስ ወያእምሩ ቦቱ ዘይመጽእ በዓለም ሠናይ ወእኩየ ወይንበሩ በተዓቅቦቱ እምኵሉ ነገር እስከ ለዓለመ ዓለም አሜን።

 

      ፩ኛ ኮከብ ዓውደ ሆይ ሓመል ክፍሉ ምሥራቅ

 

፩ ሲወጣ፤ ለዜና መፍቀድ አንተ ሰው፤ የፈለግሀው ታገኛለህ ልብህን የሚኣስደስት መልካም ነገር መጣልህ ሓሳብህ ተፈጽሞልሃልና አትፍራ አትደንግጥ ስለ ትዕግሥትህ ያለ ሕሳዌ ነገርህ ሁሉ የታመነ ሁኗል። ሰላምና ክብር ጸጋ ተመልሰውልሃልና የፈቀድሀውን ለማድረግ ተፋጠን።

 

      ፪ ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ኳራ

 

አንተ ሰው ለንግድ ተፋጠን ከቤትህ ፈጥነህ ተነሣ በፈቀድሀው ሁሉ እጅህን ብትዘረጋ ብዙ ትርፍ ታገኛለህ።

 

      ፫ ለዜና በዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሐረ ዔላ

 

አንተ ሰው፤ ወደ ንጉሥና መኳንንት ቤት ለመሔድ አትቸኵል ጊዜህ አይደለም ታገሥ ምንም ብታስብ አይፈጸምህልህምና ቸኵለህ ምንም ብታደርግ አይሆንልህም ነገር ግን ተስፋ ያደረግሀው ጉዳይ ሳታስበው በኣጋጣሚ ነገር ቶሎ ይፈጸምልሃል።

 

      ፬ ለዜና ፍትሕ ትረክቦ በባሐረ ሸኽላ    

 

አንተ ሰው፤ ነገርህ በዳኞች ዘንድ ግልጥ ሁኖ ኣይታይምና ፍርድ ለመፋረድ አትቸኩል። የራስ ሕማም ይነሣብሃልና ተጠንቀቅ።

 

      ፭ ለዜና ሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ።

 

አንተ ሰው፤ ንግድ ለመነገድ ተፋጠን። የንግድ ሓሳብህ ይፈጸምልሃል ቁጥር የሌለው ብዙ ገንዘብ ታተርፋለህ። ከሰው ጋር ኣትማከር ዝንጉ ብትሆን ግን ኪሳራ ያገኝሃል።

 

      ፮ ለዜና ተራክቦተ ሰብእ ትረክቦ በባሕረ ኣልዘዞ።

 

አንተ ሰው፤ ከሚጠላህ ሰው ጋር አትገናኝ ይህ ምክር ባትሰማ ግን ትጠፋለህ። አንተ ከእርሱ መለየት አትፈቅድም ከፍ ያለ ሰው ስለሆነ ነገርህ ሁሉ ይበዘብዝብሃልና ተጠንቀቅ።

 

      ፯ ለዜና ነጊደ ባሕር ትረክቦ በባሕረ ወንጅ።

 

አንተ ሰው፤ ንግድ ለመነገድ እስከ ፩ወር ድረስ ታግሠህ ቆይ ይህ ወር ካለፈ በኋላ ግን ፍርሓት የለብህም ተስፋህ መልካም ነው ችግርም አያገኝህም እስከ ባሕር ማዶ ብትነግድ ታተርፋለህ።

 

      ፰ ለዜና ደኃሪ ትረክቦ በባሐረ ጎጃም።

 

አንተ ሰው፤ አሁን ያሰብሀው ነገር አይሆንም ተድላና ደስታ ይጠብቁሃል በኋላ ጊዜም ብዕልና ክብር ታገኛለህ ሓሳብህ በሙሉ ይሠምርልሃል።

 

      ፱ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሐረ ዳጐ።

 

አንተ ሰው፤ ለኑሮ ያሰብሃትን ሴት ለማግባት አይሆንልህም ነገርኩህ አገርዋንም አትቅረበው ሚስትህና ሲሳይህ ለባዕድ ይሆናሉ። ፩ ነገር ከእግዚአብሔር ታዞብሃልና የቤትህም ሰዎች አታስወጣ።

 

      ፲ ለዜና ተሣይጦ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ።

 

አንተ ሰው፤ ገንዘብና ሲሳይ ለማግኘት አትፈልግ እግዚአብሔር በፈቀደው ጊዜ ራሱ ይመራሃልና ታገሥ ከምትፈልገውም ገንዘብ ጋር ያገናኝሃል በሓሳብህ ለንግድ ብትወጣ ግን ድካም ብቻ ሁነህ ያለ ትርፍ ትመለሳለህ።

 

      ፲፩ ለዜና ደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን።

 

አንተ ሰው፤ ገንዘብህ ከሰው ጋር አትቀላቅል እንዲባረክልህ በደመ በግዕ ጨምረህ ኣኑረው። የብርሀ ሣጥን እየከበረ ይሔዳል ገንዘብ በገንዘብ ላይ ታገኛለህ በተድላና ክብር ትኖራለህ።

 

      ፲፪ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ።

 

ኣንተ ሰው፤ ሆይ ወደ አሰብሀው መንገድ ኣትሒድ አይቀናህምና ታገሥ ከቤትህ ሁነህ የፈለግኸው ታገኘዋለህ በዚሁ መንገድ ቀማኞችና ኪሣራ አለውና ዛሬም የሔዱት ሰዎች ሁሉ መከራና ሓዘን ብቻ ይዘው ይመለሳሉ።

 

      ፲፫ ለዜና ገይስ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ።

 

አንተ ሰው፤ ውጭ አገር የሔደ ሰው በመዘግየቱ ክፉ አያገኘውምና አትዘን። ጥቂት ግዳጅ አግኝቶ ይዘገያል እንጂ በሰላም ይመለሳል በቅርብ ጊዜ የመምጣቱ ወሬ ትሰማለህ።

 

      ፲፬ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ግምብ።

 

ታሟል ስለተባለው ሰው እግዚአብሔር ጤናው ይመልስለታልና አትዘንና አትደንግጥ ከጥቂት ቀን በኋላ በእርሱ ትደሰታለህ።

 

      ፲፭ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ።

 

አንተ ሰው፤ እግዚአብሔር ፈቅዶ በሰጠህ በአለህበት ቦታ ተቀመጥ ወደ ሌላ ቦታ ለመሔድ ያሰብሀው ግን የመከራ በር ነውና በአለህበት አገር ኑር። ይህን ምክር ልብ አድርገህ ብትጠብቀው ይጠቅምሃል።

 

      ፲፮ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ

 

አንተ ሰው፤ ይህ ዛሬ ያሰብሀው ጋብቻ፤ መከራ ዕንቅፋት ሓዘን አለበትና ታገሠው ኋላ ግን በእግዚአብሔር ረድኤት ታሸንፋለህና ተግተህ ጸልይ ሓሳብህም ተነሥተህ በፍጥነት ትፈጽመዋለህ።

 

            ፪ኛ ኮከብ ዓውደ ሓውት ሠውር።

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቅድ ክፍሉ ምዕራብ ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ በምትፈልገው ነገር ዓጸባና ምንዳቤ ያገኝሃልና ብትተወው ይሻልሃል። ይህን ያሰብሀው ነገር ከማድረጉ መተው ይሻልሃል ታገሥ። ለነፍስህ አስብ ያስብሃትን ሴትም ጤና አታገኝምና ያለ ድካምና ልቅሶ የምታተርፈው ነገር ከቶ የለብህም።

 

      ፪ኛ፤ ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ ያሰብሀው ንግድ ይቅርብህ እኔ ተወው እልሃለኁ ዛሬ ከመነገድ ብትታገሥ ይሻልሃል ገንዘብህም ይበዛልሃል ይህ ነገር በዚሁ ፋል ተጽፏልና የቸኰለ ሰውም በግምባሩ ተደፍቶ በኪሳራ ላይ ይወድቃል።

 

      ፫ኛ፤ ለዜና በዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ። አንተ ሰው፤ የኣቴትህና (ዕድልህ) የሞገስህ ነፋስ ነፍሷል ዛሬ ፈጥነህ ወደ ንጉሡ ቤት ግባ ጊዜህ ነውና በዚሁ ቀን ፈጥነህ ግባ። ዛሬ የደስታህ ወራት ስለሆነ አትዘግይ እልሃለኁ።

 

      ፬ኛ፤ ለዜና ተፋትሖ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። አንተ ዛሬ፤ እፋረደዋለኁ ለምትለው ነገር ታገሠው ወደ ዳኛ ፊትም አትቅረብ ባለጋራህን በሽማግሌ መንገድ ብትይዘው ግን በዕርቅ ታሸንፈዋለህ ገንዘብህንም ከእነ ወለዱ ይገባልሃል ታገኘዋለህ።

 

      ፭ኛ፤ ለዜና ሠይጥ ትረክቦ በባሕረ አልዘዞ (አዘዞ)።

አንተ ሰው፤ እሸጣለኁ እለውጣለኁ አትበል” ክፉ ጊዜ ነውና ሓሳብህን ተወው መንገድህ ጥቁር ጨለማ ነው ከገንዘብህ ጋር በትዕግሥት ብትቀመጥ ይሻልሃል።

 

      ፮ኛ፤ ለዜና ተራክቦተ ሰብእ ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ አገኘዋለኁ ያልሀው ለመልካም አይደለምና አይሆንልህም። ለልብህ የትዕግሥት ስንቅ ስጠው እንጂ ለመገናኘቱ ከቶ አትሒድ። ባትገናኘው ላንተ መልካም ነው እምቢ ብትለኝ ግን ጥፋትህ ከራስህ ነው።

 

      ፯ኛ፤ ለዜና ንግደተ ኢየሩሳሌም ትረክቦ በባሕረ ጐጃም። አንተ ሰው፤ ወደ ኢየሩሳሌም (ባሕር) ለንግድ ብትሔድ መልካም የዕድልህ ጊዜ ነውና ጨክነህ ሒድ በደኅና ደርሰህ ያሰብሀውን አግኝተህ ብዙ ትርፍ ይዘህ ተደስተህ በደኅና ትመለሳለህ።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ። አንተ ሰው፤ የተመኘሀው ነገር አያምርብህም ወደ ክፉ ይለወጣልና ታገሠው በሓሳብህ ብቻ ይደር ከይህ በኋላ ግን መልካም ነገር የሆነ ሁሉ ራሱ ይመጣልሃል።

 

      ፱ኝኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ሐይቅ። አንተ ሰው፤ ያንተው ፋል ፈጥኖ ተናግሮአልና ንብረትህ (ዕድልህ) ያማረ መልካም ጥቅም ያለው ሁኖአል ዛሬ በትጋት የሚፈልግ ያሰበውን ኑሮ ያገኛልና በልብህ ጠንክረህ ፈልግ።

 

      ፲ኛ፤ ለዜና ተሣይጦ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ ከመሸጥና መግዛት ራቅ ዛሬ ገንዘብ የወደድህ እንደሆነ ሓዘን ያገኝሃል በአጠገብህ ካሉ ሰዎችም ጋር ቢሆን ከቶ ለንግድ አትቅረብ ለጊዜው የገንዘብ ፍቅር ይቅርብህ።

 

      ፲፩፤ ለዜና ደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሽማዝቢ። አንተ ሰው፤ ገንዘብህን ከሸሪክ ጋር ብትቀላቅለው ይህ መልካም ነው በችኰላ ማድረጉ ግን በትንሽ ነገር ሳያሳዝንህ የሚቀር አይመስለኝምና ታግሠህ ነገሩን ሁሉ መዝነው።

 

      ፲፪፤ “ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። አንተ ሰው፤ ወደኣሰብሀው ነገር ፈጥነህ ተነሣ እንጂ አትዘግይ። መንገድህ መልካም ነው ይቀናሃል። አብረውህ የሔዱት ግን ይጸጸታሉ።

 

      ፲፫፤ “ለዜና ገይስ ትረክቦ በባሕረ ግንብ።” አንተ ሰው፤ በይህ ጊዜ የወጣ አይመለስም። በጣም ርቆ ሒዷልና የዘመዶቹም ፊት አያይም በፈቃደ እግዚአብሔር ተለይቷል ይህም የፍጡራን አምላክ ትክክለኛ ፍርድ ስለ ተፈጸምበት ነው።

 

      ፲፬፤ “ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ተከዚ።” አንተ ሰው በሽተኛህ ይድናል ተነሥቶም ይደሰታል። ወደ ሞት ከቀረበ በኋላ እንደገና ብዙ ዘመን ተሰጥቶታልና እግዚአብሔርን ስለ አዳነልህ በትዕግሥት ዓውቀህ አመስግነው።

 

      ፲፭፤ ” ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ።” አንተ ሰው፤ በዚሁ ጉዞ ወደ ፈለግሀው ፈጥነህ ሒድ ብዙ ገንዘብና ጥቅም ታገኛለህ ሓሳብህ ሌላ ሴት (አገር) ይከጅላልና አሁን ያለችው ምሽትህን አትተዋት። አጋጣሚህና ዕድለኛህ ናት።

 

      ፲፮፤ “ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ፃና። አንተ ሰው፤ እኔ ግን አስቀድመህ ይህን መጽሓፍ እይ እልሃለኁ። ከይህ በኋላም ያሰብሀውን ጋብቻ ተወው። በጣም የሚያስፈራና የሚያስደነግጥ ግቢ ነው። መልካም አይደለም እርስዋን ብታገባት ረዥም ሓዘንና ልቅሶ ያገኝሃልና ተጠንቀቅ።

 

          ፫ኛ ኮከብ ዓውደ ሰውት ገውዝ ክፍሉ ሰሜን። ለመፍቀድ።

 

      ፩ኛ፤ ” ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ዔላ።” አንተ ሰው፤በፍቅድ አሳቢ ሆይ፤ ይህች ግዳጅህን ተዋት ለምታስበው ነገር መንገዱ ጭንቅ ነው ከማድረጉ መተው ይሻልሃልና ታገሥ። መልካም መስሎህ የምታስበው ሁሉ ይደመሰስብሃል እጅግ ክፉ ነው ይቅርብህ።

 

      ፪ኛ፤ “ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ሸህላ።” አንተ ሰው፤ የንግድን ነገር ለማወቅ የተነሣህ መርማሪ ሆይ፤ ዛሬ እነግዳለኁ ብለህ አታስብ ምንም ጥቅም እንደማታገኝበት አስታውቅሃለኁ ለጊዜው ብትተወው ይሻልሃል።

 

      ፫ኛ፤ ” ለዜና በዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ።” አንተ ሰው ወደ ንጉሥና ወደ መኳንንት ፊት ለመቅረብ አስበሃልና አይሆንልህም ይህ ቀን ካለፈ በኋላ ግን ወደ ፈለግሀው ግባ ሓሳብህም ሁሉ በፍጥነት ሊፈጸምልህ ይችላልና ቅረብ እጅ ንሣ በደስታ ይቀበልሃል።

 

      ፬ኛ፤ “ለዜና ተፋትሖ ትረክቦ በባሕረ አልዘዞ።”ኣንተ ሰው፤ ይህ ነገር እንደ ኣመድ የበነነ ነው ቢረዝምም ኃይሉ ስለደከመ ፈጥነህ ተነሥተህ ከባለጋራህ ጋር ተፋረድ። ኣንተ ታሸንፈዋለህ። ፊትህ ሲበራም በብዙዎች ሰዎች ዘንድ ትልቅ ግርማ ታገኛለህ ዛሬውኑ ረትተሀው ትገባለህ።

 

      ፭ኛ፤ ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ ንግድ ይሆንልሃል ምርኮ እንዳገኘ ሰው ገንዘብ ታገኛለህ። ይህ ሠኣት ክፍልህ ነው የፈቀድሀውን ብትገዛና ብትሸጥ ብትለውጥ የደስታህ ጊዜ ነውና ፈጥነህ ስራህን ኣከናውን እንጂ ኣትታክት።

 

      ፮ኛ “ለተራክቦ ንጉሥ ወመኰንን ትረክቦ በባሕረ ጐጃም።” ኣንተ ሰው ዛሬ ፈጥነህ ወደ ንጉሥ ኣደባባይ ሒድ ያሰብሀው ነገር ይፈጸምልሃል የንጉሡ ባለቧሎች በደስታ ይቀበሉሃልና ፊትህም እንደ መስከረም ኣበባ ይደሰታል ምን ጊዜም ቢሆን ሰላምና ሃብት እንጂ ዕንቅፋት ኣያገኝህም። ነገርንም ሁሉ በጸሎትና ትዕግሥት ያዘው።

 

      ፯ና “ለዜና ነጊደ ኢየሩሳሌም (ባሕር) ትረክቦ በባሕረዳጎ።” ኣንተ ሰው፤ ዛሬ ያሰብሀው መንገድ ለመፈጸሙ ኣትቸኵል፤ ነገር ግን እስከ ፩ወር ወይም ዓመት ድረስ ትዕግሥትን ገንዘብ አድርገህ እግዚአብሔርን ለምን የለመነ ይድናልና ሁሉም ነገር ይቀናለታል።

     

      ፰ኛ፤ “ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ።” ኣንተ ሰው ይህ ለኋላ ጊዜ ይሆነኛል ብለህ የምታስበው ነገር ከቶ ኣይሆንልህምና የሰው መሳቅያ ሁነህ እንዳትቀር ከይህ ሓሳብህ እንድትርቅ እነግርሓለሑ።

 

      ፱ኝና፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሐረ ኄኖን።” አንተ ሰው ” ይህ ለኑሮዬ ይሆነኛል ያልሀው ከቶ ኣይሆንልህም ገንዘብ ብታወጣው ጠፍቶ መቅረቱን ዕወቀው። እምቢ ብትለኝ ግን በኋላ ጊዜ ሓዘንህን ለብቻህ ትሸከመዋለህ።

      ፲ኛ፤ “ለዜና ተሣይቶ ትረክቦ ሰባረ ሸማዝቢ።” ኣንተ ሰው ለንግድ ኣስበሃልና ጥቂት ጊዜ ብትታገሥ ብዙ ጥቅም ታገኛለህ መልካም ነገር ተገልጦልሃል ያሰብሀውን ፈጽመው እጅግ የጣፈጠ የእንጀራ ኣዝመራ መጥቶልሃል ፈጥነህ ሰብስብ አትታክት።

 

      ፲፩፤ “ለዜና ደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ።” ኣንተ ሰው ገንዘብ ከሰው ጋር ለመቀላቀል ያሰብሀው ሸሪክነት ይቀርብህ ወዳጄ ነው የምትለው ሊከዳህ አስቧልና ከእርሱ መራቅ ይሻልሃል ይህ ነገር ለሙግትና ኪሳራ መሆኑን ኣስተውል ኣስቀድሜ ነገርኩህ ተጠንቀቅ።

 

      ፲፪፤ “ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ግምብ።” አንተ ሰው፤ ለመሔድ ያሰብሀው መንገድ ለጊዜው ታገሥ እግዚኣብሔር እስኪኣቀናልህ ድረስ ጸጥ በል ኣትቸኵል። ከይህ ወር በኋላ ግን ቀን ብትለውጥ መልካም ነገር ይመጣልሃል መንገድህም የቀና ይሆናል።

 

      ፲፫ኛ፤” ለዜና ዘጌሠ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ። አንተ ሰው፤ ሩቅ ሀገር የሔደው ዘመድህ መንገዱ ቀና ሁኖለታልና ወደ ኣገሩ ለመምጣት ተነሥቷል እንጀራና ጤና ይዞ ሊመጣልህ ነው ቤቱን ኣስናድተህ ቈየው። ኣብረውት የሔዱ ሁሉ፤ እንደ የእርሱ ያለ ክብር ኣላገኙም።

 

      ፲፬ኛ፤ “ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ዓባዊ። አንተ ሰው ይህ የታመመ ዘመድህ የሞት መንገድ ተከትሎታልና ወዮለት ይጠንቀቅ ንስሓ ገብቶ ስጋ ወደሙ ይቀበል። የሞተ ፍርድ የተፈረደበት ይመስላል። ወደ መዋቾች ዘመዶቹ ይናፍቃል ነገር ግን ምሕረቱ እጅግ ብዙ ስለሆነ፤ ወደ እግዚአብሔር ጸልይለት።

     

      ፲፭፤ “ለዜና ግዒዝ ትርክቦ በባሕረ ፃና።”አንተ ሰው፤ ካለህበት ቦታ ታግሠህ ቆይ በመታገሥህም ሰላምና ደስታ ከብዙ ጥቅም ጋር ታገኛለህ።ይህም ነገር በግልጥ የታወቀ የፋልህ ትርጓሜ ስለሆነ በልብህ ኣኑረው። ይህ የዕድልህ ጊዜ ፈጥኖ ቀርቧልና በትዕግሥትህ መዝግያ ቈልፈህ ያዘው።

      ፲፮ኛ፤”ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ኳራ።” ኣንተ ሰው፤ ያሰብሀው ጋብቻ እጅግ መልካም ነውና ፈጥነህ ፈጽመው የመጋባትህ ጊዜ ነው ለድግሱ ተዘጋጅ መልካም ዜና ያማረ ጤና ከዕድሜ ጋር አለው ፈጥነህ ካደረግሀው ምንም ዕንቅፋት የለብህም።

 

      ፬ኛ ኮከብ ዓውደ ሰውት ሽርጣን ክፍሉ ደቡብ ለተፋትሖ።

     

      ፩ኛ፤ “ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ሸህላ።” አንተ ሰው፤ ያሰብሀውን ለመፈጸም ትንሽ ታገሥ ኣትቸኵል ተስፋ ያደረግሀው ነገር ታገኘዋለህና ትዕግሥትህን ኣስቀድም ያሰብሀውን ሁሉ ራሱ ፈጥኖ ይመጣልሃል። በምስጋና ተቀበለው።

 

      ፪ኛ፤”ለነጊደ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ።” ኣንተ ሰው፤ ለንግድ ፈጥነህ ተነሣ ብዙ ጥቅም ይጠብቅሃል እግዚአብሔር ፊቱን መልሶልሃልና ወደ ኣሰብሀው መንገድ ሒድ ዛሬ የዕድልህ ጊዜ ነው ፋልህ በግልጽ ያስታውቃል።

      ፫ኛ፤ “ለበዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ አልዘዞ።” ኣንተ ሰው፤ በይሁዳ ዘመን መልካም ነገር ያጋጥምሃልና ፈጥነህ ወደ ንጉሥና መኳንንት ቤት ግባ ማናቸውም ነገር ብትፈልግ ታገኛለህ ወራቱ ያንተ ኣባይያ ነው።

 

      ፬ኛ፤ “ለዜና ተፋትሖ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ።” ኣንተ ሰው፤ ፍርድ ለመፍረድ ኣትቸክኵል እስከ ፩ ወር ታገሥ እስኪያልፍ ድረስ እጅህን ለጠላትህ ኣሳልፈህ እንዳትሰጥ። ነገርህን በልብህ ሠውረህ ያዝ ከ፩ ወር በኋላ ግን ለመፍረድ ፈጥነህ ተነሣና ድሉ ያንተ ነው ይፈረድልሃል።

 

      ፭ኛ፤”ለዜና ሠይጥ ትረክቦ በባሕረ ጐጃም።” አንተ ሰው፤ ለመነገድ ያሰብሀው ነገር ዛሬ በትዕግሥትት የያዝሀው እንደሆነ ችግርህ ሁሉ ይቃለላል ሓሳብህም ይፈጸምልሃል በረከትና ሞገድ ከአንተ ጋር ነው።

 

      ፮ኛ፤ “ለተራከቦት ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ።” ኣንተ ሰው፤ ወደ ንጉሥ ቤት ለመግባት ኣትቸኵል ታገሥ ጊዜው ይርቅብኛል ብለህ ኣትጨነቅና ኣትጠራጠር ንጉሡ ፈልጎ አስጠርቶ ወስዶ በክብር ይሾምሃል ይሸልምሃል።

      ፯ኛ፤ “ለነጊደ ኢየሩሳሌም (ባሕር) ትረክቦ በባሕረ ሓረቅ።” ኣንተ ሰው፤ በሕሊናህ ጨክነህ ባሕር ለመሻገር ካሰብህ መንገድህ ያማረ ነው። ምንም መሰናክል የለውም በነፍስና በሥጋ የምትጠቀምበት ነገርም ይቆይሃና ፈጥነህ ሒድ።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን።” አንተ ሰው፤ መልካም ነገር መጣልህ እግዚአብሔር ከክፋ ነገር ሁሉ ይጠብቅሃል ፍጻሜህም ያማረ ይሆናል።

 

      ፱ኝኛ፤ “ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ።” አንተ ሰው፤ ዛሬ ፈጥነህ ተነሣ ያማረና የተወደደ መዝገብ ይቆይሃል ኑሮህም መልካም ነው ኣዘውተረህ ዳዊት ድገም ብዙ ጥቅም ይጠብቅሃልና ዝግ አትበል።

 

      ፲ኛ፤ “ለዜና ተሣይጦ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ።” ኣንተ ሰው፤ ለመሸጥ ለመግዛት ኣትቸኵል በመንገድህ ልቅሶ አለ ዝግ ብትል ግን ባሰብሀው ገባያ ብዙ ጥቅም ታገኝበታለህ።

 

      ፲፩ኛ፤ “ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ግምብ።” አንተ ሰው፤ ገንዘብህ ከወዳጅህ ጋር ለመቀላቀል አስበሃልና ፈጥነህ ተሻረከው ንጹሕ እሙን ሰው ነው ብዙ ጥቅምም ታገኛላችኁ።

 

      ፲፪፤ “ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ተከዜ።” አንተ ሰው፤ በአንተ ላይ ተመቅኝተው የተነሡብህ አሉና በዚች ጊዜ መንገድ አትሒድ ብትሔድ ግን ፍርሓትና ድንጋፄ ይቆይሃል። ብትታገሥ ደግሞ በትዕግሥትህ ጠላቶችህን ድል ትመታቸዋለህ።

     

      ፲፫ኛ፤ “ለዜና ገይስ ትረክቦ በባሐር ዓባይ።” አንተ ሰው፤ የምትፈልገውን ሰው ከብዙ ቀን በኋላ በደኅና ወደ አገሩ ይመጣልሀል ፈልጌ አመጣዋለኁ ብለህ ብትሔድ ግን ብዙ ዕንቅፋትና ችግር ይቆይሃልና ከቶ አትሒድ ብትታገሥ ይሻልሀል።

     

      ፲፬፤ “ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ጣና።” አንተ ሰው፤ በታመመው ሰውህ ከቶ አትፍራና አትዘን ከደዌው ድኖ ፈጥኖ ይነሣል። ነገር ግን ስለ በሽታኛው እግዚአብሔርን እያመሰገንህ ስለ እርሱ ምጽዋት ለነዳያን ስጥለት።

 

      ፲፭ኛ፤ “ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ኳራ።” አንተ ሰው ካለህበት ቦታ ወይም ሥራ ፈጥነህ ውጣ ፋልህ (ዕድልህ) ተገልጿልና ምክንያት ሳታበዛ ቸኩልህ ሒድ ዛሬ ነፃ ውጣ ከነበርህበት በቶሎ ልቀቅ።

 

      ፲፮፤ “ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ዔላ።” አንተ ሰው፤ እግዚአብሔር ፈቅዶ መልካም ምሽት እንኪአጋጥምህ ድረስ ታገሥ። ይህ ያሰብሀው ጋብቻ ብዙ ችግርና ሕውከት  አለበትና ዛሬ አትፈጽመው። እርስዋ ፈቅዳ ነበር ዘመዶችዋ ግን ምክንያት ሁነው አልፈቀዱምና መታገሥ ይሻልሀል ትቅርብህ።

 

            ፭ኛ ኮከብ ዓውደ ታው አሰድ ክፍሉ ምሥራቅ

 

 

      ፩ኛ፤ “ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ።” አንተ ሰው ያሰብሀው ለማግኘት ለጊዜው የተጠበቀ ሁኗል አሁን አትአገኘውም የእምትሠለጥንበት ጊዜ ገና ነው። ረዢም ጊዜ ትተክዛለህ ሓዘንህን በትዕግሥትና ጸሎት ካሳለፍሀው በኋላ ግን እርሱ አምላክህ የመልካም ነገሮች በር እንደገና ይከፍትልሃል።

 

      ፪ኛ፤ “ለዜና ንግድ ትረክቦ በባሕረ አለዛዞ።” አንተ ሰው፤ ለንግድ ጥቂት ቀን ታገስ ዝግተኛ ሁን አትቸኩል ገንዘብህን ለንግድ ብታወጣው ትርፍ የለም ድካም ብቻ ይዘህ ትመለሳለህ።

 

      ፫ኛ፤ “በዊአ ቤት ንጉሥ ወመኳንንት ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ የእግዚአብሔር ፈቃድ እስኪሆን ድረስ ላሰብሀው ነገር ሁሉ ከመቸኰል መታገሡ ይሻልሃል። ትካዜም እንዳያገኝህ ልብ አድርገህ ነቅተህ ጸልይ።

 

      ፬ኛ፤ “ለተፋትሖ ፍትሕ ትረክቦ በባሕረ ጐጃም።” አንተ ሰው፤ ጠላትህ ትንሽ መስሎ ቢታይህም ንቀህ አትከራከረው ለዓይን የሚያስከፋና ለጆሮ የሚቀፍ ክፉ ስም ያከናንብሃል ኃይልህንም ያደክመዋል ብርቱ ጠላት ነው የተነሣብህ ያሳፍርሃል። ስለይህ ታገሥ ቢሆንልህ ግን ብትታረቅ ይሻልሀል።

 

      ፭ኛ፤ “ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ።” አንተ ሰው ንግድ ለመነገድ ገንዘብህ እንዳታወጣ እልሃለኁ እንዳትከስር ተጠንቀቅ  የዕድልህ ሲሳይ አንተ ሳታውቀው በሌላ ምክንያት በሰላም ይመጣልሃል።

 

      ፮ኛ፤ “ለተራክቦተ ሰብእ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ።” አንተ ሰው፤ በእግዚአብሔር ስም አማፅንሃለኍ እገናኘዋለኍ ብለህ ከአሰብሀው ሰው ጋር ከቶ እንዳትገናኝ አንተ ለመገናኘቱ ልብህ ተሰቅሏል እርሱ ግን ልበ-ጽኑ ስለሆነ ብትገናኘውም ያሳዝንሃል እንጂ አያስደስትህም። በአፉ ይደልልሃል ከጠላቶችህ ጋር ሆኖም  ያማሃልና አትቅረበው።

 

      ፯ኛ፤ “ለዜና ነጊደ ኢየሩሳሌም ትረክቦ በባሕረ ኄኖን።” አንተ ሰው ይህች ዘመን ፍርሓትና ዓጸባ ችግርና ምንዳቤ የበዛባት ናትና በመርከብ ባሕር ተሻግረህ አትሒድ። የተነገረልህን ምክር ብትጠብቅ ግን በመሚጣው ዓመት ሒደህ ክብርና ደስታ ታገኛለህ።

 

      ፰ኛ፤ “ለዜና ደኃሪ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ።” አንተ ሰው፤ በኋላ ዘመን እንዲያምርልህ የምታስብ ሰው ሆይ፤ የሻሀውን ነገር ዛሬ እንድታገኘው ፈጥነህ ተነሥ ሁሉም ተከናውኖልሃልና ሓሳብህን ሳታስረዝም ሳትፈራ ነቅተህ የፈቀድሀውን ስራ።

 

      ፱ኛ፤ “ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ።” አንተ ሰው፤ መታገሥህ መልካም ነው ለንብረት ያሰብሀው የታመነ ነው ከ፰ ቀን በኋላ መልካም ይገጥምሃል ነገር ግን በጣም አትቸኩልበት የቸኮሉ ሰዎች ስንት የጠፉ ይመስልሃል!።

 

      ፲ኛ፤ “ለዜና ተሣይጦ ትረክቦ በባሕረ ግምብ።” አንተ ሰው፤ የዕድልህ ፋል ዛሬ ጊዜህ አይደለምና እነግዳለኍ ብለህ ገንዘብህን አታውጣ ይልሃል። ሠዓቱ የደፈረሰ ነው። ነገር ግን በእግዚአብሔር  ብትታመን ፍጻሜ የሌለው ብዙ ሃብት ለወደኋላ ታገኛለህ።

 

      ፲፩፤ “ለዜና ደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ተከዚ።” አንተ ሰው፤ የታገሠ መልካም ነገር ይቆየዋልና ከቶ አትቸኩል። የቸሎለው ኋላ ይጸጸታል እስከ ፩ ወር ድረስ የትዕግሥትህ ቀኖች ይሁኑ ምክሬን ካለመስማትህ ገንዘብህ ከሰው ጋር ብትቀላቀለው ግን የያዝሀውን ታጣለህል።

 

      ፲፪ኛ፤ “ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ዓባይ።” አንተ ሰው፤ በ፩ ሰው ምክንያት ያልታሰበ መልካም ነገር ታገኛለህና ፈጥነህ ከቤት ወጥተህ ሒድ በሰላምም ትመለሳለህ።

 

      ፲፫ኛ፤ “ለዜና ገይስ ትረክቦ በባሕረ ጣና።” አንተ ሰው፤ ስለ የሔደው ሰው የምትጠይቀኝ እርሱ ዘመኑ ተፈጽሞ በመቃብር ውስጥ ዓርፏል። ለእርሱ እንዘንለት መልኩም ጠፍቷልና በእርሱ ፈንታ የሚሆንህ ሌላ ሰው ፈልግ።

 

      ፲፬ኛ፤ “ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ኳራ።” አንተ ሰው፤ ይህ በሽተኛህ ደዌው ጽኑ ነውና ሳትቸኵል መድኃኒት ፈልግለት ቢጸናበትም እስከ ፰ ቀን ነው እንጂ ይድንልሃል።

 

      ፲፭ኛ፤ “ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ዔላ።” አንተ ሰው ካለህበት ቦታና ስራ የወጣህ እንደሆነ ፍርሓትና ድንጋፄ ችግርና መከራ ያገኝሃልና ለመውጣት አትቸኵል እስከ ፩ ዓመት ድረስ ባለህበት ቆይ ዛሬ ብትቸኵል ግን ለዘወትር ስትጸጸት ትኖራለህ።

 

      ፲፮ኛ፤ “ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ።” አንተ ሰው፤ ይህ ያሰብሀው ጋብቻ እስከ ጥቂት ጊዜ አቆየው የሚል ፋል መጣልህ። ብዙ ሰዎች በቅንአት ያሙሃልና ያውም ለጥቅምህ ይሆናል እንጂ ምንም አይጐዳህም።

 

      ፮ኛ፤ ኮከብ ዓውደ ኖን ሰንቦላ ክፍሉ ምዕራብ።

 

      ፩ኛ፤ “ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ አለዘዞ።” አንተ ሰው፤ ከይህ ቀደም የነበረው ግዳጅህ በጭንቅና በምንዳቤ ነበር ዛሬ ግን ይቅርታ አግኝተሃል ብዙ ምርኮና ደስታ መጣልህ ሓሳብ ተፈጽሟልና ከእንግዲህ ምንም ችግር አያገኝህም።

 

      ፪ኛ፤ “ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ።” አንተ ሰው፤ ዕወቅ ልብ አድርግ ባሁኑ ሠዓት ንግድ ይቅርብህ የገንዘብ ጥፋት ያገኝሃል ሓሳብህም ሁሉ ከመቅጽበት ይፈጸምልሃል።

 

      ፫ኛ፤ “ለዜና በዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ጐጃም።” አንተ ሰው ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም አሁን ወደ ንጉሥ ቤት ብትገባ እጅግ መልካም ነው ከእርሱ የምትፈልገው ሁሉ በደስታ ይሆንልሃል በትልቅ ስራ ላይ ሹመትና ሽልማት ታገኛለህ ነገር ግን ወደ ንጉሡ ቤት ለመግባት የፈጠንህ እንደሆነ ነው።

 

      ፬ኛ፤ “ለዜና ተፋትሖ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ።” አንተ ሰው፤ ጠላትህን በክሕደቱ ሓፍረት ታለብሰዋለህ  አንተ ግን ነገርህ ሁሉ ተዘጋጅቷልና ያሰብሀውን ነገር በፍጥነት ታገኘዋለህ አንተ ረትተሀው እንደምትገባ ፋልህ ተገልጿልና ወደ ፍርድ ቤት ሒደህ ተሟገተው።

 

      ፭ኛ፤ “ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ።” አንተ ሰው፤ ሽጥ ለውጥ አትጠራጠር እንዳትከስር ፍርሓት በልብህ አታግባ። በቅርብ ጊዜ ከደስታ ጋር መልካም የሆኑ ብዙ ትርፍ ይዘህ ትገባለህ። ብትጠራጠር ግን ነገርኩህ ትጠፋለህ ቶሎ ተፋጠን።

 

      ፮ኛ፤ “ለዜና ተራክቦ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን።” አንተ ሰው ለአንተ ተስፋና በረከት የሆነ ነገር ቀርቦልሃልና ወደርሱ ሒድ ተገናኘው የሚያስደስት ፋል ወጣልህ ምንም ቤት የምትሰራበት ጊዜ ቢመጣ ወዳጅህ ግን በልቡ ቂም ይዞብሃልና አትፍራ ከቤተ ክርስቲያን አትለይ እምብዛም አትመነው።

 

      ፯ኛ፤ “ለዜና ነጊደ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ።” አንተ ሰው፤ ልብህ ባሕር ኢየሩሳሌም ለመሔድ ቢፈልግ ሓሳብህ ነውና ተፋጠን ትጠቀማለህ ደስ ይበልህ ዛሬ ባሕር ተሻግሮ መሔድን በማናቸውም ምክንያት አትተወው ብቻ ተፋጠን።

 

      ፰ኛ፤ “ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ።” አንተ ሰው፤ ይህ ፋልህ መልካም ሽታ የሚመስል ዜና ያለው ነው። እስከ መጨረሻው የምሥራች የሞላበት ጊዜህ ነው  ያሰብሀው ደስታ ይፈጸምልሃል ምንም ቢሆን ትንሽ የገንዘብ ጥፋትና ሑከት አይቀርብህም።

 

      ፱ኛ፤ “ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕር ግምብ።” አንተ ሰው፤ እኔ ግን ጥፋት አለውና ተጠንቀቅ አትቅረብ አልሁህ። በኑሮህ ብዙ ፍልስፍና ገብቶበታልና መከራና ችጋር እንዳይገኝህ ተጠበቅ። ወደ ይህ ጥቅም ወደ የሌለው ኑሮ ወደ ድኽነትና ዓጸባ ከቶ አትቅረብ እልሃለኍ።

 

      ፲ኛ፤ “ለዜና ተሣይቶ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ።” አንተ ሰው፤ ለንግድ የገዛሀው እቃ ረጋ ብለህ ብትሸጠው በቅርብ ጊዜ ትጠቀምበታለህ አሁንም ገብያህ ይቀናልና የፈቀድሀውን ግዛ። ፈጠን በል በቃልህና በምግባርህም የታመንህ ሁን።

 

      ፲፩፤ “ለዜና ደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ።” አንተ ሰው፤ ገንዘብህን አደራ ለማስቀመጥ ወይም ከሺርካ ጋር ለማቀላቀል ብታወጣው ቀልጦ መቅረቱን ዕወቀው። ምክርህም እንዳይበተንብህ ተጠንቀቅ ነፍስህን አታበሳጭት ሓሳብህንም ለውጥ።

 

      ፲፪ኛ፤ “ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ጣና።” አንተ ሰው፤ እስከ ፩ ወር ድረስ ታገሥ ከይህ በኋላ ግን እግዚአብሔር መንገድህን አቅንቶ ይጠብቅሃል። አትቸኩል ጥቂት ታገሥ የሚል መልካም ፋል ወጥቶልሃል ምክርህም ከፍ ያለ ይሆናል።

 

      ፲፫ኛ፤ “ለዜና ገይስ ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ የምሥራች እልሃለኍ የወጣውን ዘመድህ ፊቱ እንደ ጨረቃ ደምቆ እንደ ንጋት በርቶና አምሮ በደስታ ይገባልሃል።

 

      ፲፬፤ ” ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ዔላ።” አንተ ሰው፤ በታመመው ዘመድህ የሞት ፍርድ ተፈርዶበታል ነገር ግን እግዚአብሔር ኃጢአቱ ይቅር ቢልለት ገንዘቡን ለነዳያን እየመጸወትህ ለምንለት ጊዜ ሞቱ ደርሷልና ሒድ ገንዘው።

 

      ፲፭፤ “ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ።” አንተ ሰው፤ ከአለህበት ቦታ ለመልቀቅ ወዳጅ መስለው ጠላቶች መክረውብሃልና ልብህን አታጥፋ ትላንትና በቅርብ ጊዜ ስለ ምን አሰብሀው? ይቅርብህ ክፉ ምክር ነው።

 

      ፲፮ኛ “ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። አንተ ሰው፤ ይህ ዛሬ ያሰብሀው ጋብቻ ዕድሜህ ልክ እንደ እሳት ሲያቃጥልህ ለመኖር ነውና ይቅርብህ ራቀው። ሸንጋዮች፤ ይህ ጋብቻ እንደ ፀሓይ የሞቀ እንደ ጨረቃ የደመቀ ነው ቢሉህ ከቶ አትመናቸው። ሊያታልሉህ የተላኩ ናቸውና እርገማቸው እንዲያውም በእርግጫ መትተህ አባርራቸው።

 

           ፯ኛ ኮከብ ዓውደ ካፍ ሚዛን ክፍሉ ሰሜን

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ረጋ ያልህ ያልቸኰልህ ሁን የምትፈልገው መፍቅድ የተጠበቀ ነው አምላክህ ፈቅዶ ሲሰጥህ እንጂ ዛሬ በመቸኰልህ አታገኘውም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ከርሱ የበዛና የከበረ ብዙ ሀብት አምላክ ይሰጥሃል።

 

      ፪ኛ፤ “ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ጎጆኣም።  አንተ ሰው፤ ዛሬ ጥፋት አለውና ለንግድ አትቸኵል ከ፰ ቀን በኋላ ግን በመታገሥህ መልካምነገር ሊኣጋጥምህ ነው ነግድ።

 

      ፫ኛ፤ “ለዜና በዊአ ቤት ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ አንተ ሰው፤ ዛሬ ወደ ንጉሥ ቤት ብትገባ ክፉ ነገር አያገኝህም ነገር ግን ከ፪ቀን በኋላ ብትገባ የለመንሀው ሁሉ ይሰጥሃል። እርሱም በሕዝቡ ዘንድ የተመሰገነ ይሆናል።

 

      ፬ኛ፤ ” ለዜና ተፋትሖ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። አንተ ሰው በክፋቱ ልብህን ለሚኣስጨንቀው ባለጋራህ ለመፋረድ ኣትቸኵል። እስከ ፩ ወር ድረስ ታገሠው ከይህ በኋላ ግን ሙሉ ጤናና የድል ጥቅም ታገኛለህ። ችግርህም ሁሉ ኣምላክ ያቃልልሃል።

 

      ፭ኛ፤ ለዜና ሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። ኣንተ ሰው፤ በያዝሀው የንግድ እቃ የክፉ ሰዎች ኣንደበት ለክፎሃልና ገንዘብህ በከትንቱ እንዳታጠፋ ወራቱ እስኪኣልፍ ድረስ እንደ ተኛ ሰው ምሰል። ይህ ወራት ካለፈ በኋላ ግን የእግዚአብሔር ረድኤት ስለ አልተለየህ ፊትህን ወደ ደስታ መልሰህ ንግድህ ብትቅጥል ብዙ ትርፍ ታገኛለህ ኣትጠራጠር።

 

      ፮ኛ፤ ለዜና ተራክቦ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። ኣንተ ሰው፤ ለመገናኘት ካሰብሀው ሰው ጋር ራቅ ኣትቅረበው እስከ ፪ ወር ድረስ የቀና መንገድ ይገለጽልሃልና ወደ እርሱ ከቶ አትሒድ እርሱ ወደ አንተ ቢመጣ ግን በሰላም ተቀበለው እንጂ ከቶ የጠብ ምልክት ኣታሳየው።

 

      ፯ኛ፤ “ለዜና ነጊደ ኢየሩሳሌም ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ።” አንተ ሰው ወንድሜ ሆይ ባሕሩ ጸጥታ እንስኪኣገኝ ድረስ ታገሥ በሁለተኛው ዓመት ግን ሒድና ነግድ። የታገሠ ከሁሉ ይድናልና በመንገድህም መሰናክል አያገኝህም።

 

      ፰ኛ፤ “ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ግምብ።” ኣንተ ሰው ይህ ሓሳብህን እስከ ፩ ዓመት ድረስ ተወው ያቺን ሃገር ብዙ ሰዎች ቢመኙዋት ሊኣገኟት አልቻሉምና ኣንተም ከዛው ሓሳብህ ተመለስ ምክሬንም ኣምነህ ተቀበለው እልሃለኍ።

 

      ፱ኛ፤ “ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ተከዚ።” ኣንተ ሰው፤ በይህ በምታስበው አኗኗር ጤና ታገኛለህ ደግ ነገር ልክ የሌለው ደስታ ይመጣልሃል። ከቤተ ክርስቲያን ኣትለይ ጸልይ መጽውት።

 

      ፲ኛ፤ “ለዜና ተሣይጦ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ።” ኣንተ ሰው፤ ሓሳብህ የሚፈልገው እስክታገኝ ድረስ ጥቂት ቀን ታገሥ ጥቂት ከመታገሥህ በኋላ ግን ንግድህና ስራህ ሁሉ ኣንጥረኛ እንዳነጠረው ጥሩ ቀለመ ወርቅ ይሆንልሃል።

 

      ፲፩ኛ፤ “ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ጣና።” ኣንተ ሰው፤ ደስ የሚያሰኝህ የምሥራች ፋል መጥቶልሃልና ገንዘብህ ለማቀሳቀሱ ኣትፍራ ብዙ ትርፍ ታገኛለህ ሓሳብህ ሁሉ ይፈጸምልሃል ዘመኑ ዘመነ ረሃብ ሊሆን ነው ላንተ ግን የደስታህ ጊዜ ስለሆነ ገንዘብህን ፈጥነህ ቀላቅለው።

 

      ፲፪፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ ዛሬ በምታስበው መንገድ ዕንቅፋት አለውና ተወው ኣትሒድ ክፉ ምቀኛ እንደሚቈይህ ፋልህ ተናግሯልና ተጠንቀቅ።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ገያሲ (ኸያጅ) ትረክቦ በባሕረ ዔላ። ኣንተ ሰው፤ ክፉን ወይም መልካም አግኝቶት ይሆንን? የምትለው ሰው እርሱ ለመምጣት ይቸኵላልና ከጥቂት ቀን በኋላ ወደ ቤትህ መጥቶ በርህን ክፈትልኝ ይልሃል።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ሸህላ። አንተ ሰው፤ ያ የታመመብህ ሰው በእግዚሓብሔር መንገድ የሚመላለስ ስለሆነ ባለ መድኃኒቶችን ሳይፈለግ ኣሁን ድኖ ሊነሣልህ ነውና ኣትስጋ።

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ (ጉዞ) ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። አንተ ጻድቅ ሰው ሆይ ይህ ዛሬ የምታስበው ጉዞ ፩ወር እስኪያልፍ ድረስ አትቸኵልበት። መልካም ነገር ኣያገኝህምና ለጠላቶችህ መሣቅያ እንዳትሆን ተጠንቀቅ።

 

      ፲፮ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ኣለዛዞ። ኣንተ ሰው፤ ለመጋባት ቸኵል ሙሉ ደስታ ኣለውና በልብህ ጻፈው ለማድረጉም ፈጠን በል ሴትዋ ቸኵላለችና ከእርስዋም ብዙ ብዙ መልካም ነገር ታገኛለህ።

 

          ፰ኛ ኮከብ ዓውደ ዛይ ኣቅራብ ክፍሉ ደቡብ

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ጐጃም። አንተ ሰው፤ ይህ ያሰብሀው መፍቀድ መልካም አይደለምና ታገሠው ምንም አታገኝበትም ፈጽመህ ተወው ነገርህን ለማንም ሳታካፍል ፍላጎትህ ሁሉ ተግተህ ለእግዚአብሔር ብቻ ንገረው።

 

      ፪ኛ፤ ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ። አንተ ሰው የዛሬ ንግድ የገንዘብ ጕድለት አለው ከእሚነግዱ ሰዎች ጋር ኣትቅረብ ራቃቸው። ወንድሜ ሆይ፤ ባትነግድ ግን ገንዘብህን ከማጥፋትና ከፍርሓት ከክርክርና ጥርጣሪ ትድናለህ ይህም ዘመን የችግርና የኪሳራ ጊዜ ነው።

 

      ፫ኛ፤ለበዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። ኣንተ ሰው፤ ዛሬ ከንጉሥ ዘንድ መልካም ነገር ታገኛለህ ይመስለኛል ስለይህም ፈጥነህ ወደ ንጉሥ ቤት ሒድ። ተስፋ ካደረግሀውም ሌላ ብዙ ሥልጣንና ሃሳብ ይሰጥሃል።

 

      ፬ኛ፤ ለዜና ተፋትሖ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ ፋልህ ከጠላትህ ጋር ለመፋረድ ዛሬ ኣትቅረብ ይልሃል እርሱን የመሰለ ክፉ ከቶ አይገኝምና ለጊዜው ተጠንቀቅ።

 

      ፭ኛ፤ ለዜና ሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። አንተ ሰው፤ እሸጠዋለኍ ብለህ የምታስበው ገንዘብ ጉድለትና ጥፋት አለውና ከመሸጡ ተመለስ። አንተ ከእርሱ ተስፋ የምታደርገው ሰላም ብቻ እንዲሰጥህ እንዚአብሔርን ለምነው እንጂ በፋልህ በኩልስ እንጃ አይመስልም አትሽጥ።

 

      ፮ኛ፤ ለዜና ተራክቦተ ሰብእ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። ኣንተ ሰው፤ ለመገናኘት ያሰብሀውን ሰው ተወው ከእርሱ የምታገኘው ነገር ከድካምና ልፋት በቀር  ምንም አይጠቅምህምና ራቅ። እንዲያውም ባንተ ላይ ክፉ ሲመክርብህ ኣድሮኣልና ከቶ ኣትቅረበው እንዳያጠፋህ።

 

      ፯ኝ፤ ለነጊደ ኢየሩሳሌም (ባሕር) ትረክቦ በባሕረ ግምብ። አንተ ሰው፤ ዛሬ የክብርህ ወራት ደርሷል። ምንም ሳትፈራና ሳታመነታ ፈጥነህ ፈቃድህን ፈጽም ኣትደር ኣትዘንጋ። ይህ ወንጌላዊ የዕድልህ ኣጋጣሚ የደስታህ ጊዜ ነው።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ትከዜ። አንተ ሰው፤ ይህ ያሰብሀው ነገር የጥርጣሪ በር አበጅለት እልሃለኍ። የዚህም ፋል ትርጓሜው አስቸጋሪ ስለሆነ ተስፋ ከምታደርገው ነገር ሁሉ እግዚአብሔርን እየለመንህ ቆይ።

 

 

      ፱ኝኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕር አባዊ (አባይ)። አንተ ሰው ይህ የምታስበው ኑሮ ከሓሳብ በቀር ምንም የሚፈጸም ነገር የለውምና ታግሠህ ተጠበቅ። ለመቀመጥ ፈቅደህ ስታስብ አድረሃልና ከይህ አሳብ ተመለስ የሚኣስጨንቅ ነገር እንዳያገኝህ የይህ የምክሬን ነገር ተጠንቅቀህ አስብበት።

 

      ፲ኛ፤ ለዜና ተሣይጦ ትረክቦ በባሕረ ጣና። አንተ ሰው፤ ለመነገድ ታስባለህ ነገር ግን ገንዘብ ይጠፋብሃል። በልብህ እስክትመረምረው ድረስ ተጠበቅ። ይህም በቅርብ ቀን ምልክቱ ታገኘዋለህ። ከይህ በኋላ ግን ገብያ ሊኣጋጥምህ ነው።

 

      ፲፩ኛ፤ ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ ከሺርካህ ጋር ገንዘብ ለመቀላቀል የምታስበው ነገር እስከ ፩ ወር ድረስ ተወው። ጕድለት አለበት። ኣንተ ግን ገንዘብህ የሚበረክትልህ ይመስልሃልና ምክሬን ባትሰማም አለ ምክንያት ትጠፋለህ።

 

      ፲፪ኛ፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ ይህ የዛሬው መንገድህ ማሳለፍያ እንደማታገኝ ሁኖ ተዘግቶብሃልና ታገሥ። እጅግ የሚኣስፈራና የሚኣስደነግጥ አደገኛ ስለሆነ ለጊዜው ይቅርብህ።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ገያሲ ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ። ኣንተ ሰው፤ ወደ ውጭ አገር የሄደው ዘመድህ በሰላም ይገባልሃልና ስለ እርሱ ኣትፍራ። ወዳጄ ሆይ ኣንተም ኣለ እርሱ መኖር ኣይሆንልህምና እስኪገባልህ ድረስ ታገሥ ኣይዞህ ነገር ኣያገኘውም በእርሱ ኣትሰቀቅ።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። ኣንተ ሰው፤ በጠና በሽታ ላይ በኣለው ዘመድህ በመድከሙ ይሞታል ብለህ ኣትፍራ ጥቂት ታገሥ እልሃለኍ እግዚኣብሔርን እየለመንህ መድኃኒት ፈልግለትና ይድናል።

 

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ኣልዘዞ። ኣንተ ሰው፤ ካለህበት እወጣለኍ ብለህ አታስብ ብዙ ክፉ ነገር እንዳይቈይህ ተጠበቅ ከክፉ ልትድን ከሓሳብህ ተመለስ። ብትወጣ ግን ጠጠት ከኣልሆነ በቀር ምንም መልካም ነገር ኣታገኝም።

 

      ፲፮ኛ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። ኣንተ ሰው፤ ይህ ጋብቻ ብዙ ጭንቅና ችግር ኣለበትና ይቅርብህ። በትዕግሥትህ ዕድሜ እንድታገኝ ለጊዜው በገረድ ተቀመጥ ከይህ በኋላ ግን መልካም ጋብቻ በመልካም ትዕግሥት ታገኛለህ።

 

            ፱ኝኛ ኮከብ ዓውደ ድንት ቀውስ ክፍሉ ምሥራቅ

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ። አንተ ሰው፤ ዛሬ ለማታገኘው ሃብት መቸኰል ይቅርብህ ይህ ፈቃድህ ከማድረግ ብትመለስ ግን ትድናለህ ኋላ እንዳትጠጠት ታገሥ።

 

      ፪ኛ፤ ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። ኣንተ ሰው ይህ ንግድህ ጥቅምና ጤና የለውምና ጥቂት ጊዜ ታግሠህ ቆይ ሁሉን በእጁ ለያዘ አምላክ ለምነው ከመከራም ትድናለህ።

 

      ፫ኛ፤ ለዜና በዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ ወደ ንጉሥ ቤት ለመግባት በኣሰብሀው ሓሳብ የፈቀድሀውና የተመኘሀው መልካም ነገር ሁሉ ታገኛለህ። ከንጉሥም ዘንድ ክብርና የዕድል አሸናፊነት ይገጥምሃል። በግቢው ውሥጥ ሁሉ ያሠለጥንሃል።

 

      ፬ኛ፤ ለዜና ተፋትሖ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። ኣንተ ሰው፤ ፍርድ ለመፋረድ ኣትቸኵል ኋላ እንዳትጠጠት ኣትቸኵል የታገሠ ክፉ ነገር ኣያገኘውምና እስከ ፩ ወር ድረስ ቆይ። ብትቸኵል ግን ምንም ጥቅም ኣታገኝም ኣልሃለኁ።

 

      ፭ኛ፤ ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። ኣንተ ሰው፤ ልትሸጠው ያሰብሀው ነገር እስከ ፩ወር ድረስ አቆየው። ከይህ በኋላ ግን ልብህ እንደ ፈቀደው ዕጽፍ ትርፍ ታገኝበታለህና ቸኵለህ ኣትሸጥ።

 

      ፮ኛ፤ ለዜና ተረክቦ ትረክቦ በባሕረ ግምብ። አንተ ሰው፤ አሁን ያሰብሀው መገናኘት ጠብ የሚፈጥር ነውና ጥቂት ታገሠው ከመታገሥህ በኋላ ግን መልካም ጥበብና የበሽታ መድኃኒት የሚገኝበት ስለሆነ በጥልቅ ጥበብና ፍቅር ብትገናኘው ትጠቀምበታለህ።

 

      ፯ኛ፤ ለነጊደ ኢየሩሳሌም ትረክቦ በባሕረ ተከዜ። አንተ ሰው ሆይ፤ እስከ ፩ ዓመት የታገሥህ ሁን ከዓመት በኋላ ግን በአገርህ ውስጥ ወይም ባሕር ተሻግረህም ቢሆን ብትሔድ ትጠቀማለህ ፍርሓትና ድንጋፄ ተወግዶልሃል የጓደኛህም ምክር እንደ ክርስቶስ ቃል እመነው።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ። አንተ ሰው፤ ጤና ስለ ተሰጠህ ሰው ሁሉ ፊቱን ወዳንተ መልሷልና ክፉ ያገኘኛል ብለህ አትሥጋ ወደ ኋላም ያማረ ነገር ሁሉ ይመጣልሃልና በምስጋና ተቀበለው።

 

      ፱ኝኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ጣና። አንተ ሰው ለወጠንሀው ኑሮ ፍርሓት የለብህምና አትዘን አትጨነቅ ጥቅምና ሲሳይ ካንተ አይለይም ግልጥ የሆነ ያማረ ኑሮ ሁኖልሃል ለማድረጉ ዛሬ ፈጥነህ ተነሣ።

 

      ፲ኛ፤ ለተሣይጦ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው ልትሸጠው በአሳብሀው ነገር ፍርሓትና ጥርጣሪ አታግባ። ብዙ ጥቅም አለውና ዛሬሽጠው ለምሥራችህ የተመደበ የደስታህ ጊዜ ደርሷልና ፈጠን ብለህ ሽጠው።

 

      ፲፩ኛ፤ ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ ከባለእንጀራህ ጋር ገንዘብህን ብትቀላቅለው ፋልህ ተናግሮኣልና ብዙ ትርፍ ታገኛለህ። ይህ ነገር እንዳያመልጥህ አስብባትን ክፍልህ በሸሪክነት ነው። እምቢ ብትለኝ ግን በክፉ ድኽነት ላይ ትወድቃለህ ነገርሁህ።

 

      ፲፪ኛ፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ። አንተ ሰው፤ ይህ መንገድ ብዙ ድካምና ጭንቅ ያለበት ነውና ወደ አሳብሀው ሃገር እስከ ፩ ወር ድረስ አትሒድ። የታገሠ ከመከራ ያመልጣል።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ገይስ (ኼያጅ) ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። አንተ ሰው፤ ወደ ውጭ የሔደው ዘመድህ አሁን ይመጣልሃል ሓሳቡ ተፈጽሞለታልና አይዘገይም አንተ የምትሰጠው የለህም  እንጂ ከጥቂት ቀን በኋላ ይገባል።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ አልዘዞ። አንተ ሰው ስለ የታመሙ ዘመድህ ብትጠይቀኝ ዕድሜው አልቋልና ብዙ ድካም ስላለው ወደ ዘለዓለማዊ ቤቱ ሸኘው። ሞት ተልኮ ዛሬ ወደ ቤቱ ይገሰግሳል ነገር ግን ኃጢኣቱን ይቅር ይልለት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለምንለት።

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ ይህ ፋልህ የምሥራች ያለው ድንቅ ጉዞ ነውና እንዳሰብሀው በይህች ቀን ፈጥነህ ጉዞህን ጀምር። ምኞትህ የሚፈጸምበት እንደ ደወል ድምፅ ያማረ ደስታና ክብር የተጐናጸፈ ጉዞ ሁኖልሃል።

 

      ፲፮ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ጎጆኣም። አንተ ሰው፤ የተመኘሀው ጋብቻ  አሁን ታገኘዋለህና ለመፈጸሙ ቸል ኣትበል ይህችም ሴት ፊትዋ እንደ ፀሓይ የበራ ነው። ጤናና ደስታ እንጀራና ዕድሜ ታገኛለህ ጋብቻህን ፈጥነህ ፈጽመው ዕድለኛህ ናት።

 

            ፲ኛ ኮከብ ዓውደ ጤት ጀዲ ክፍሉ ምዕራብ

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። አንተ ሰው፤ ይህችን ፍላጎትህ እስከ ዓመት ተዋት ለጊዜው ጐደሎ ናትና ትቆይልህ። በኋላ ግን በመልካም ተቀበላት የታገሠ መልካም ነገር እንደሚኣገኝ ፋልህ ገልጾ ተናግሮኣል።

 

      ፪ኛ፤ ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ መልካም ነገር ታገኛለህና ሒድ ነግድ የምሥራች የሚነግር ፋል ወጥቶልሃል እግዚአብሔር የፈቀደልህ ብዙ ትርፍ እንድታገኝ ፈጠን ፈጠን ብለህ ነቅተህ ነግድ አትታክት።

 

      ፫ኛ፤ ለዜና በዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። አንተ ሰው፤ ከእርሱ የተመኘሀው ምኞትህ ሊፈጸምልህ ነውና ዛሬ ፈጥነህ ወደ ንጉሥ ግባ ላንተ ብቻ ቸር ነው ትልቅ ማዕረግ ይሰጥሃል ፈጥነህ የክብርህ ምሥራች ትሰማለህ።

 

      ፬ኛ፤ ለዜና ተፋትሖ (ፍርድ) ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። አንተ ሰው፤ ዛሬ ከባላጋራህ ለማፋረድህ አትቅረብ ይህ ወር አጋጣሚህ አይደለምና በቀጠሮ አሳልፈው ይህ የዓመጸኞች ወር ካለፈ በኋላ ግን ምንም ከክፉ ሳትፈራ ጠላትህን ተፋረደው የርሱ ነገር የጐሰቈለና የጠፋ ሁኗልና ትረታዋለህ።

 

      ፭ኛ፤ ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ግምብ። አንተ ሰው፤ ሓዘንና ችግር የሌለው ፋልህ ወጥቷልና ሒድ ሽጥ ለውጥ ይህን የመሰለ አጋጣሚ የለም ያላሰብሀው ብዙ ትርፍ ይዘህ ትገባለህ።

 

      ፮ኛ፤ ለዜና ተራክቦ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ። አንተ ሰው ለመገናኘት ካሰብሀው ሰው ጋር የሚከለክልህ ችግርና ዕንቅፋት ተወግዷልና ሒደህ ፈጥነህ ተገናኘው ፋልህ እንደ ሙሉ ጨረቃ የደመቀ ሁኖ ወጥቷል ሓሳብህን ወደ ኋላ አትመልስ ተገናኘው።

 

      ፯ኛ፤ ለነጊደ ኢየሩሳሌም (ባሕረ) ትረክቦ በባሕረ ዓባይ። አንተ ሰው ፤ መንገድህ በጭንቅ የታጠረ ሁናልና ታግሠህ ቆይ። በይሁ ዓመት ባሕር የሚሻገር ሁሉ ሓዘን ብቻ እንጂ ትርፍና ደስታ አያገኝም። እምቢ ብለሀኝ ብትሔድ ግን ፤ ጥፋትህን በራስህ ላይ ነው።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ፃና። አንተ ሰው፤ ይህ ለንግድ ያሰብሀው ነገር መልካም ሁኖ አይታየኝምና አትሽጥ አትግዛ ትንሽ ቀን ብትታገሥ ይሻልሃል። አንተ ግን ለኋላ የምትጠቀምበት ወራት መስሎ ይታይሃልና ተጠንቀቅ። መከራ እንዳያገኝህ ከይህ ሓሳብህ ራቅ ጊዜህ አይደለም።

 

      ፱ኝኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ ይህ ለኑሮ ይሆነኛል ብለህ ያሰብሀው ሩቅ የሆነ ሓሳብ፤ ድካምና ጻዕር የሞላበት ጥቅም የማታገኝበት ነውና እስከ ፩ ዓመት ታገሠው። ከዓመት በኋላ ግን፤ ያሰብሀው ነገር ሁሉ በጥበብ ታገኘዋለህ።

 

      ፲ኛ፤ ለተሣይጦ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ ይህ የንግድህ በር ኣፍ ፩ ወር እስኪፈጸም ድረስ ዘግተህ ያዘው። ትዕግሥት የጌትነት ሁሉ ደጅ ስለሆነ ጤናም ጭምር ታገኛለህና ብትታገሥ ይሻልሃል ተወው አትግዛ።

 

      ፲፩ኛ፤ ለዜና ደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ። አንተ ሰው፤ ከባለ እንጀራህ ጋር ገንዘብህን ለመቀላቀል የምታስበው አሳብ ለልብህ አያስደስተውና እስከ ፩ ዓመት ድረስ ፈጽመህ ተወው። ቂምና በቀል ያመጣብሃልና ከቶ አትቸኵልበት።

 

      ፲፪ኛ፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። አንተ ሰው ምኞትህ ፋል ለመፈጸሙ ከእግዚአብሔር ዘንድ ተፈቅዶልሃል።  ከማሸነፍ ጋር ቀንቶህ ብዙ ትርፍ ይዘህ በደስታ ትመለሳለህና ወደ ፈቀድሀው መንገድ ሒድ ዛሬ ውጣ አትደር።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ገያሲ ትረክቦ በባሕረ አልዘዞ። አንተ ሰው፤ በቤትህ ወጥቶ ወደ መንገድ የሔደው ዘመድህ ፊቱ እንደ ፀሓይና ጨረቃ በርቶ ስንቱን አስደሳች ነገር ይዞ በዝግታና በቀጥታ በሰላም ይመጣልሃል።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ መልካም ፋል መጥቶልሃልና በታመመው ሰውህ አትፍራ ቀኝ ጐኑን የሚያመው በሽታ ተወግዶለታል የሚኣስጨንቀው ርኩስ መንፈስም ከእርሱ ይርቃል የደኅንነት መንፈስ ከጤና ጋር ተሰጥቶታል።

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ጎጆ-ኣም። አንተ ሰው፤ እስከ ፩ ዓመት ድረስ ረዢም ጉዞ አታድርግ እግዚአብሔር ጤናነት የሰጠህ እንደሆነ ተነሥተህ ተጓዝ። ከዓመት በፊት ያስፈራሃልና ስለ እግዚአብሔር ከቤትህ አትውጣ እልሃለኁ። እምቢ ብትለኝ ግን በኋላ ትጠጠታለህ።

 

      ፲፮ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ። አንተ ሰው ይህ ያሰብሀው ጋብቻ የጻዕር ቤት ነውና የታገሥህ ሁን። ምናልባት ምልክት ታገኝበታለህና እስከ ፪ ወር ቆይ ከዚያ በኋላ ታሸንፋለህ የደከምህበትም ድካም ሁሉ ፍሬው ታገኘዋለህ ብቻ ዝግ ያልህ ሁን።

 

            ፲፩ኛ ኮከብ ዓውደ ጻዴ ደለዊ ክፍሉ ሰሜን

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ ይህ ፈቃድህ ከእግዚአብሔር ዘንድ የምሥራች ሁኖ ተሰጥቶሃልና ቤተ ክርስቲያን ሒደህ ምስጋና አቅርብ ምኞትህ ተፈጽሞልሃል አላገኘውም ብለህ ከቶ አትዘን።

 

      ፪ኛ፤ ለነጊደ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። አንተ ሰው፤ ለንግድ ስራ ልብህ ከ፪ ተከፍሏል በ፩ ልብ ተነሥተህ አምላክን አምነህ ሳትወላወል ፈጥነህ ነግድ። ከነጋዴዎች መካከል ያማረ መልካም ዕድል ተሰጥቶሃል። ምኞትህ ሁሉ ታገኘዋለህና ሳትፈራ በእምነት ነግድ።

 

      ፫ኛ፤ ለበዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። አንተ ሰው፤ በንጉሥ ቤት የእንጀራ አዛዧ ለመሆን ዕድል ገጥሞሃልና ከ፪ ቀን በኋላ ግባ ፈጥነህ ሒድ በደስታ ይቀበልሃል። ጻድቅ ንጉሥ ነው ያምንሃል።

 

      ፬ኛ፤ ለዜና ተፋትሖ ትረክቦ በባሕረ ግምብ። አንተ ሰው፤ ባላጋራህ የእስር ቤት በር እየመታ ገብቶ ሊታሰርልህ ነውና ፈጥነህ ሒደህ ተፋረደው ከመቅጽበት ትረታዋለህ። ይህን ለአደረገልህ ልዑል እግዚአብሄርንም በጣም አመስግነው።

 

      ፭ኛ፤ ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ። አንተ ሰው፤ አሁን ያለው ንግድህ ጥቅሙ ለዛሬ ትንሽ ነውና አትሽጠው እስከ ፪ ወር ድረስ ብታቈየው ግን ዕፅፍ ትርፍ ታተርፍበታለህ። ይህ የሚሆነውም በረቂቅ አእምሮና በቀጭን ሕሊና ጠብቀህ ብትከታተለው ነው።

 

      ፮ኛ፤ ለዜና ትራክቦ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ። አንተ ሰው፤ ዘመድህን ዘግይተህ ነው እንጂ ፈጥነህ አትገናኘውም አንተ ግን አገኘው ወይም ኣጣውን ይሆን? በማለት ከሒሳብ አትድንም። እርሱ ደኅና አለ ስላንተም ሁሉ ጊዜ ይጠይቃል። አምላክ በፈቀደው ቀን ትገናኛላችኁና አትጠራጠር።

 

      ፯ኛ፤ ለነጊደ ኢየሩሳሌም ትረክቦ በባሕረ ጣና። ኣንተ ሰው፤ እጅግ ያማረ መልካምም የሆነ የሚያስደስት እጅ መንሻ ታገኛለህና ምንም ሳትጠራጠር ፈጥነህ ሒድ ተሻገር እልሃለኁ።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ በይህ ፋል ጥቅም ይገኝን ይሆን? ብለህ በልብህ አትጠራጠር እኔ እልሃለሁ በኋላ ጊዜ የሚኣስደስት ታገኛለህ ይህ ነገር የታመነ ነው።

 

      ፱ኝኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ ለዘለዓለማዊ ኑሮህ የሚሆን መልካም ጠቃሚ ነገር ታገኛለህና ፈጥነህ ተነሣ። ምክሬን በትዕግሥት ብትሰማ ከቶ ክፉ ነገር እንደእምኣያገኝህም እመነኝ።

 

      ፲ኛ፤ ለተሣይጦ ንዋይ ትረክቦ በባሐ ሸኽላ። አንተ ሰው፤ ለመሸጥ ለመለወጥ ተነሥ ፈጠን በል ቸኵልበት ዛሬ ብዙ ትርፍ የእምታገኝበት ገብያ እንደሚኣጋጥምህ ፋልህ የምሥራች ይልሃል።

 

      ፲፩ኛ፤ ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። አንተ ሰው፤ የምትጠራጠረው ነገር ተወግዶልሃልና ገንዘብህ ከሸሪክ ጋር ለመቀላቀል አትዘግይ ፍላጎትህ ለማግኘትም ለማድረጉ ቸኵል።

 

      ፲፪ኛ፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ አልዛዞ። አንተ ሰው፤ ሕሊናህን በጸሎትና በንስሓ አሳድረው እንጂ እሔዳለኁ አትበል መንገድህ ከክፉ የከፋ ስለ ሆነ እስከ ፩ ወር ታገሠው። ከ፩ ወር በኋላ ግን የታዘዘብህ መከራ ተወግዶልሃልና ተነሥተህ ሒድ መንገድህም ይቀናል።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ገያሲ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ ይህ ከቤቱ የወጣ መንገደኛ ወደ አንተ ለመምጣት ሲል ሕሊናው እንደቆመ ነው። ወንድሜ ሆይ ከብዙ ሃብትና ደስታ ከጤና ጋር አምላክ በፈቀደው ቀን ሊመጣልህ ነውና አትቸኵል እልሃለኁ።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ጎጆ ኣም። አንተ ሰው፤ በበሽተኛው ዘመድህ ሁኔታው ያልታወቀ ሓዘን አለብህ እስከ ፪ ወር አጥብቃችኁ ጸልዮለት። ስለእርሱ የሚሆነው ነገር ግን የእግዚአብሔር ሓሳብ ብቻ ያውቀዋል።

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ። አንተ ሰው ከአለህበት ቤትና ስራ ለመውጣት የምታስበው ሓሳብህ ሁሉ በእግዚኣብሔር ላይ ጣለው። ነገር ግን ሓሳብህ መልካም ስለሆነ በፊተኛው ምክርህ ሒድ ኣታመናታ። አምላክ ይፈጽምልሃልና ፈጥነህ ውጣ።

 

      ፲፮ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። አንተ ሰው፤ ለማግባት ያሰሃትን ሴት ኣትተዋት ተነሣ ፈጥነህ ወደ እርሱዋ ሒድ ይህች እንደ ፀሓይ የበራች ደም ግባትዋ ያማረ ጠባይዋ የሠመረ ናት ሌሎች ሳይቀድሙህ አግባት ብዙ ክብርና ጤና ከልጆች ጋር አለላችኁ።

 

            ፲፪ኛ ኮከብ ዓውደ ጠይት ሑት ክፍሉ ደቡብ።

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። ወንድሜ ሆይ ይህ የምትፈቅደው ነገር አታገኘውም ታጣዋለህ። ነገር ግን ያሰብሀው ጉዳይ እግዚአብሔር ፈቅዶ እንኪሰጥህ ድረስ ታገሥ ዛሬ የሚሻልህ ጸሎትና ንስሓ ብቻ ነው።

 

      ፪ኛ፤ ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። አንተ ሰው፤ በይህ ንግድ ብዙ ትርፍ ታገኛለህና ፈጥኖ የሚያስደስትህ ንግድ ከብዙ ትርፍ ጋር ታዞልሃል ልብህም ደስ ደስ ይለዋል።

 

      ፫ኛ፤ ለዜና በዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ግምብ። አንተ ሰው፤ ወደ ንጉሥ ቤት ለመግባት ያሰብሀው ሓሳብ መልካም ነው ተነሥተህ ፈጥነህ ግባ። ጠላትህም ሙቶልሃልና ዛሬ እጅግ መልከ መልካም ነገር ሊኣጋጥምህ ነው።

 

      ፬ኛ፤ ለተፋትሖ ፍትሕ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ። አንተ ሰው ከክፉ ሰው ጋር ተጣልተሃልና ተጠበቅ ፍርድ ለመፋረድ አትቸኩል። የጠመደህም እጅግ ክፉ ባለጋራ ስለሆነ ከቶ አትቅረበው በመታገሥህም ዋጋህን አታጣም።

 

      ፭ኛ፤ ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ። አንተ ሰው፤ ንግድ ጠርቶሃል ሒደህ ሽጥ ለውጥ ብዙ ትርፍ ከቦሃልና እንድታገኘው ፍጠን ዕድልህ ምንኛ መልካም ነው።

 

      ፮ኛ፤ለዜና ተራክቦ ትረክቦ በባሕረ ጣና። አንተ ሰው፤ ለመገናኘት ያሰብሀውን ሰው ተግተህ ተገናኘው እርሱ አጥብቆ ይወድሃል አይንቅህም መገናኘትህ መልካም ነው ሹሞ ሸልሞ ይሰድሃል።

 

      ፯ኛ፤ ለነጊደ ባሕር ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ ባሕር ለመሻገር ስለ አስብሀው ሓሳብ ጥቂት ብትቆይና ወራቱም ብትብተው ደግ ነበር። አብረውህም ከሚሔዱ ሰዎች ጋር መልካም ነገር ታገኛላችኁ።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ ለኋላ ጊዜ የሚሆነው ነገር ለማወቅ ከ፰ወር በኋላ ጠይቀኝ ያን ጊዜ ሓሳብህ ሁሉ ይፈጸምልሃል ነገር ግን ሳትወላውል ፈጥነህ ኋላ ብታደርገው እጅግ መልካም ነው።

 

      ፱ኝኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ። አንተ ሰው፤ ስለ ንብረትህ በምታስበው ነገር ለኋላ እንዲኣምርልህና እንዲሠምርልህ እስከ ፩ ዓመት ድረስ ዳዊት እየደገምህ በጸሎት ተጸምደህ ታገሥ። ሓሳብህ አገኘው ወይም አጣውን ይሆን? እያለህ በኑሮህ ውስጥ ፍርሓት አታግባበት።

 

      ፲ኛ፤ ለተሣይጦ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። አንተ ሰው፤ አሁን ልትገዛውና ልትሸጠው ያሰብሀው ነገር ጥፋት አለበትና አትቅረብ ዓርፈህ ገንዘብህን ጠብቅ።

 

      ፲፩ኛ፤ ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ አልዘዞ። አንተ ሰው፤ ገንዘብህን ከሰው ጋር አትቀላቅል እስከ ፩ ዓመት ለሸሪክነት ያገባሀው እንደሆን ይጠፋብሃል ዝግ በል አትቸኵልበት በአለብህ ተመስገን በል።

 

      ፲፪ኛ፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ወንጂ። አንተ ሰው፤ ወደ ተገለጸልህ ሁሉ ፈጥነህ ሒድ መልካም ነገር ይቆይሃል ብዙ ጥቅም ቀርቦልሃልና እንድትደሰበት ፈጠን በል ሒድ ይቀናሃል።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ገያሲ (ዘጌሰ) ትረክቦ በባሕረ ጐጆ-ኣም። አንተ ሰው ፤ ወደ ውጭ የሔደው ዘመድህ ኣሁን ወደ ኣንተ ለመምጣት ይቸኵላል ፈጥነህ በመንገድ ታገኘዋለህ በብሩህ ገጽ ተቀበለው።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ዳጎ። አንተ ሰው እግዚአብሔር ሁሉ ጊዜ ይጠብቅሃልና የምሥራች በሽተኛው ዳነ የሚል ፋል ወጣልህ የሚኣስፈራ ነገር የለብህም አሁን በጤና ተነሥቶ ሊሮጥ ነው።

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። አንተ ሰው ቦታ ለመለወጥ የምታስበው እስከ ፩ ወር ድረስ  ቆይ ከዝያ በኋላ ግን ለመውጣት ፍጠን በኋለኛው ወር ቦታ ወይም ስራ ብትለውጥ ግን ይቀናሃል መውጣትህ ክፉ እንዳይሆንብህም እየኣታለለ የሚመክርህን ሰው ከቶ አትስማው ልትጠቀም አይወድም ጠላትህ ነው።

 

      ፲፮ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። አንተ ሰው ቦታ ለመለወጥ የምታስበው ፍጠን በኋለኛው ወር ቦታ ወይም ስራ ብትለውጥ ግን ይቀናሃል መውጣትህ ክፉ እንዳይሆንብህም እየኣታለለ የሚመክርብህርን ሰው ከቶ አትስማው ልትጠቅውም አይወድም ጠላትህ ነው።

 

      ፲፯ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ ይህ ጋብቻ የመከራ ቤት ማለት ነውና ከቶ አትቅረብ እኔ ነገርሁህ ትታመማለህ ወይም ትሞታለህ ኮከቡም ፀርህ ነው።

 

            ፲፫ኛ ኮከብ ዓውደ ዓይን ክፍሉ ምሥራቅ።

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቅድ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። አንተ ሰው አደርገዋለኁ የምትለው ስራ የሚከለክልህ የለምና ፈጥነህ አድርገው አትፍራ ትጠቀምበታለህ ወደ ኋላ የሚጠቁምህን የሰው ሕሳብ ከቶ አትስማው እልሃለኁ።

 

      ፪ኛ፤ ለዜና ነጊደ ትረክቦ በባሕረ ግምብ። አንተ ሰው ምኞትህን እንዲፈጸምልህ በይህ ወራት ፈጥነህ ነግድ አሁን መልካም ነገር ሁኖልሃል ክፉ ነገር አያገኝህም። ተስፋ ያደረግሀው የንግድ ስራ በሙሉ ሁሉ የምሥራች ሁኖልሃል።

 

      ፫ኛ፤ ለዜና በዊአ ቤት ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ። ኣንተ ሰው ንጉሥና መኳንንት ፊታቸውን ወደ አንተ መልሰዋል ከፍ ያለ ክብርና መልካም ስጦታ ቀርቦልሃል ድካም ታሸንፈዋለህ። የመከራው ሠዓት ደርሶበታልና እጅግ ደስ ይበልህ። ድል ያንተ ነው።

 

      ፭ኛ፤ ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ፃና። አንተ ሰው፤ ይህ ፋል የምሥራች ነጋሪህ ነው ለመሸጥና ለመለወጥ ፈጥነህ ተነሥ በብዙ ድካም ከፍ ያለ ጥቅም ታገኝኣለህ ንግድ ዕድልህ ስለሆነ የፈቀድሀውን ነግድ ጊዜህ ነውና ትጋ ፍጠን ኋላ ትደስታለህ።

 

      ፮ኛ፤ ለዜና ተራክቦ ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ ሊገናኝህ የመጣ ሰው ትሑት ይመስላል እንጂ ጠላትህ ነው። እርሱ ጥቅም ለሌለው መገናኘት ይቸኵላል። አንተ ግን ዝግ ብለህ ነፍስህን ጠብቅ።

 

      ፯ኛ፤ ለነጊደ ኢየሩሳሌም ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ በዚህ አገር ያሰብሀው ሓሳብ ሁሉ ትተህ ለንግድ ባሕር ተሻገር መልካም ጥቅም ታገኛለህ ምክሬን እሺ ብለህ ብትሰማው ትጠቀማለህ።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ። አንተ ሰው፤ የምሥራች የሚነግርህ ፋል መጣልህ ይህ ፋል ነውር የለበትምና በኋላ ጊዜ ለሚመጣው ዕድልህም መቅድሙ ነው ከቶ አትደንግፅ መልካም ነገር አጭቶሃል ትደሰታለህ።

 

      ፱ኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። አንተ ሰው፤ ለንብረትህ ጠባቂ የሆነ መልካም ፋል መጣልህ ፈጥነህ ተነሥ ይልሃል ለዘለዓለማዊ ኑሮህ የሚሆን የፈለግሀው ሁሉ ከነ የምሥራቹ ታገኘዋለህ።

 

      ፲ኛ፤ ለተሣይጦ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ አልዛዞ። አንተ ሰው፤ ለንግድ ጥቂት ቀን ታገሥ። ከዚህ በኋላ ግን ባለ ጸጋዎች ነን ብለው የሚመኩትን ሁሉ ድል ታደርጋቸዋለህ። እንድትጠቀም ምክሬን ተቀበል እኔ ከቶ አትግዛው እልሃለኁ።

 

      ፲፩ኛ፤ ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ ገንዘብህን ለመቀላቀል ያሰብሃቸው ሰዎች ምለው የሚበሉ ከዳተኞች ናቸውና ገንዘብህን ለብቻህ አኑር እንጂ ከአንዳቸው ጋር እንኳ ቢሆን ገንዘብህን ከቶ አትቀላቀል  ቀልጠህ እንዳትቀር ተጠንቀቅ።

 

      ፲፪ኛ፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ጐጃም። አንተ ሰው፤ ፍፁም ሞገስ ዓድሎሃልና እግዚኣብሔርን በሙሉ ልብህ አመስግነው መንገድህ የቀና የሰላም መንገድ ነው።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ዘጌሰ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ። አንተ ሰው፤ ዘመድህ ርቆ የመኖሩ ዘመን ዛሬ ተፈጸመ መገናኘታችኁ ተዳርሷል ይመጣልሃል የደስታ ዘመንም ይሆንላችኋል።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። አንተ ሰው፤ ይህ በሽተኛ የሕይወቱ መጨረሻ ሁኗል ከዛሬ ጀምሮ አይሞትም ብለህ ተስፋ አታድርግ እግሮቹ ወደ መቃብር በር ይራመዳሉ። ተስፋ የለውም አትድከም በቃህ።

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ ካለህበት አገር ፈጥነህ ውጣ መልካም ደስታ እንድታገኝ ፈጥነህ ተነሥ መቀለዴ አይምሰልህ ዛሬ ሊኣልፍልህ ነው። የመከራና የችግር ጊዜህ አልፏል።

 

      ፲፮ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። አንተ ሰው ሆይ፤ አንተ ለእርስዋ እርስዋ ለአንተ ልትሆን ተጠርታችኋልና ፈጥነህ አግባት። ሞገስህ ንብረትህ ናት ለማግባትዋ የሚከለክልህ ዕንቅፋት የለብህም። የተባረከች አቴትህ ናት።

 

             ፲፬ኛ ኮከብ ዓውደ ፌ (ፍቁር) ክፍሉ ምዕራብ።

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቅድ ትረክቦ በባሕረ ግምብ። አንተ ሰው፤ ከመልካም በቀር ክፉ ነገር አያገኝህም ሓዘንህና ትካዜህ በመልካም ተፈጸመ። ለኃጢኣትህ ይቅርታ አግኝተሃል መልካም የሚኣስደስት የፈቀድሀው ነገር ወደ አንተ ይገሰግሳልና በምስጋና ተቀበለው።

 

      ፪ኛ፤ ለዜና ነጊድ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ። አንተ ሰው፤ ነጋዴ ሆይ፤ መሳይ የሌለው መልካም ነገር ታገኛለህ ሒድ ፈጥነህ ነግድ ምኞትህ ሁሉ ዛሬ በመከር ሰብስብ አትታክትና አትሰልች እልሃለኁ።

 

      ፫ኛ፤ ለዜና በዊአ ቤተ ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ። አንተ ሰው፤ ወደ ንጉሥ ግባ በብሩህ ገጽ ይቀበልሃል ሃብትና ክብረት  ሥልጣንና ሹመት መልካም ነገር ሁሉ ተዘጋጅቶ ቀርቦልሃል ሒድ ተቀበል።

 

      ፬ኛ፤ ለዜና ፍትሖ ትረክቦ በባሕረ ጣና። አንተ ሰው፤ ከጠላትህ ጋር ከመፋረድ ራቅ ትዕቢት ተሰምቶታልና ለጊዜው አትቅረበው ጸሎት ያዝ ተጠበቅ።

 

      ፭ኛ፤ ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ የንግድ ምሥጢር ሁሉ ተገልጾልሃልና ዛሬ የፈቀድሀው ሁሉ ሽጥ ለውጥ የሚኣመልጥህ የለም መልካም ነገር ታገኛለህ።

 

      ፮ኛ፤ ለዜና ተራክቦ ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ የምትፈልገው ሰው በቅርብ ጊዜ እስከ ምኝታ ቤትህ ድረስ እየተደሰተ ይመጣልሃል። አንተም ከእርሱ ዘንድ ብዙ ደስታ ታገኛለህ።

 

      ፯ኛ፤ ለዜና ነጊደ ኢየሩሳሌም ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ። አንተ ሰው፤ ሒድ ባሕር ተሻግረህ ነግድ ለነፍስና ሥጋ የሚጠቅም ብዙ ሃብት ታገኛለህ ጠግበህ እግዚኣብሔርን እንዳትረሳውም አደራ እልሃለኁ።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። ኣንተ ሰው፤ ለዘለዓለም የሚሆንህ ደስታ ይሀውና መጣልህ የለመንሀው ተፈጸመልህ ለኋላ ጊዜ የሚሆን ያማረ መልካም ነገር ተዘጋጅቶልሃልና በትዕግሥትና ዕረፍት ሰብስበው ፍጻሜህም እጅግ ያማረ ነው።

 

      ፱ኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ አልዘዞ። አንተ ሰው፤ አሁን በጣም ያማረ ኑሮ ከብዙ ጊዜ ጀምረህ የተመኘሀው ነገር መጣልህ ፋልህ ከነየምሥራቹ በደስታ ተቀበለው።

 

      ፲ኛ፤ ለዜና ተሣይጦ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ ይህ ዛር ልትሸጠው ወይም ልትገዛው ያሰብሀው እቃ እስከ ፩ ወር ድረስ ዝም ብለህ ብትቆይ ይሻልሃል ከ፩ ወር በኋላ ግን ዕፅፍ ትርፍ እንደምታገኝበት አትጠራጠር። የዓመት ትርፍ በ፩ ቀን ታገባዋለህ።

 

      ፲፩ኛ፤ ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ጎጆ-ኣም። አንተ ሰው፤ ገንዘብህን ከባለእንጀራህ ጋር ለመቀላቀል አትመኘው።እነ እርሳቸው በ፩ነት እንነግድ ቢሉህም የኪሳራ ዕንቅፋት እንዳይመታህ እምቢ በላቸው ሓሳባቸው የሕልም ውሃ ነው። ከቶ አትቅረባቸው።

 

      ፲፪ኛ፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ዳጐ። አንተ ሰው፤ ይህ ያሰብሀው መንገድ በጣም የሚያስፈራና የሚኣስደነግጥ ክፉ ነገር አለውና ከቶ አትሒድ።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ዘጌሠ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። አንተ ሰው፤ የወጣው ሰው አሁን በሰላም ይገባል ስለ እርሱ አትፍራ አትደንግጥ አትጠራጠር ታገሥ እርሱም ወደ ኣንተ ሊመጣ ይቸኵላልና በመካከላችሁም አምላክ እንደሚመሰገን አድርጕ ናችኍ።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕመሙ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ የታመመው ዘመድህ የተግሣጽ ድካሙ አልፎለት አሁን ይድናልና ይሞታል ብለህ ፍርሓትና ጥርጣሬ አታግባ።

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። አንተ ሰው፤ ይህ ጉዞህ የሴት ምክር የተደበለቀበት የሚመስል ነውና ተወው እስከ ፩ወር ታገሥ ትካዜ ያገኝሃል ክፉ ነው።

 

      ፲፮ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። አንተ ሰው፤ ይህ ሀሳብህ የአምላክ ፈቃድ ነውና ለሴትዋ ብቻ ፈጥነህ ደብዳቤ በምሥጢር ጻፍላት በደስታ አንብባ እሺ ትልሃለች። ይህች ያሰብሃት ሴት የልብህ ደስታና ወላድ በእንጀራና ዕድሜ የተሞላች ናት ፈጥነህ አግባት።

 

                  ፲፭ኛ ኮከብ ዓውደ ጻዴ ክፍሉ ሰሜን።

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቅድ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ። አንተ ሰው፤ አደርገዋለኁ ብለህ ካሰብሀው ነገር ተጠበቅ ሓዘን ጭንቅ መከራ ያገኝሃል። አስቀድመህ ንስሓ ግባ ጸልይ ንቃ።

 

      ፪ኛ፤ ለነጊደ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ። አንተ ሰው፤ በገንዘብህ ብቻ ነገድ ብድር አትግባ አትጠራጠር ብዙ ትርፍ ታገኛለህ ምንም አትከስርም ነገር ግን አምላክ የሰላም እንጀራ ስለሰጠህ አመስግነው እንጂ እንዳትታበይበት ተጠንቀቅ።

 

      ፫ኛ፤ ለባዊአ ቤት ንጉሥ ትረክቦ በባሕረ ፃና። አንተ ሰው፤ ወደ አሰብሀው ጌታ ወይም ስራ ለመግባት አትሥጋና አትፍራ መልካም ነገር ታይቶልሃል መንገድህ የቀና ነው ፈጥነህ ግባ።

 

      ፬ኛ፤ ለዜና ተፋትሖ ትረክቦ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ ብዙ ደስታ ያለው የምሥራች እነግርሃልኁ አትፍራ ጠላትህ በክፋት ይቅሠፍልሃል። አንተ አይየለብኝ ብለህ ታዝናለህ ፈጥነህ ተፋረደው ግርማ ሞገስ ያድርብሃልና ትረታዋለህ።

 

      ፭ኛ፤ ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ እንደፈቀድሀው ሽጥ ለውጥ ብዙ ትርፍ ታገኛለህ ከጠብና ክርክር ትድናለህ ተግተህ ሥራ እኳንና አንተ አሽከርህም ያተርፋል ችግሩ ይወገድለታል በመልካም ያዘው አትናቀው ዕድለኛህ ነው አትክዳው እንዳትጠፋ።

 

      ፮ኛ፤ ለተራክቦተ ሰብእ ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ። አንተ ሰው፤ ከፈቀድሀው ሰው ጋር ተገናኝ እርሱም ተቀምጦ ይጠብቅሃል አንተን ለመገናኘት ይችኵላል ለዓይኑም ይናፍቅሃል ሕሊናው በፍቅርህ ተመስጧል በጣም ይወድሃልና አንተም ውደደው እንጂ አትጠራጠረው።

 

      ፯ኛ፤ ለነጊደ ኢየሩሳሌም ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ አንተ ሰው፤ ወደ ኢየሩሳሌም (ባሕር ማዶ) ለመሔድ ብታስብ እስከ ፩ ዓመት ቆይ ንግድህ በችኮላ ብታደርገው ዕንቅፋትና ሓዘን ያገኝሃል ከዓመት በኋላ ግን የሰላም ወራትህ ነውና ስንቅህም በዝያው ይቆይሃል ፍጠን።

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ አልዛዞ። አንተ ሰው፤ ለኋላ ጊዜ የሚሆንህ ነገር እስኪገለጽልህ ድረስ ያለ ጥርጥር የትም ገሥግስ የምሥራችህ ይፈጸምልሃል በኋላ ጊዜ በዘመነ ሽምግልናህ ከፍ ያለ ሥልጣንና ሙሉ ሃብት ታገኛለህ።

 

      ፱ኝኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ አሁን ወደ አሰብሀው ኑሮ ተነሥተህ ሒድ ምንም ክፉ ነገር አያገኝህም የደስታና የሞገስ ዕድልህ እንደ ንጋታ ኮከብ ከብቦ ወጥቶልሃል ኑሮህ ይስፋፋልሃል ልብህም ይበራል።

 

      ፲ኛ፤ ለተይሣይጦ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ጎጃ-ኣም። አንተ ሰው፤ አሁን ያሰብሀው እቃ ፈጥነህ ግዛው ቸኵልበት ያጤንሃል ያስደስትሃል። በይህ መግዛትና መሸጥ ተስፋ ያደረግሀው ነገር ሁሉ እንደሚፈጸምልህ የምሥራችህ ተናግሯል።

 

      ፲፩ኛ፤ ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ። አንተ ሰው፤ የተመኘሀው ገንዘብና ጤና ይሀው መጣልህ ገንዘብህ በመቀላቀል ብዙ ትርፍና ደስታ ታገኝበታለህ ሸሪክህ እሙን ነው ፈጥናችኁ በትጋት ስሩ።

 

      ፲፪ኛ፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። አንተ ሰው፤ የኔ ሕሊና ስላንተው ነገር ሲያስብ ነበር ሒድ ገስግሥ የፈራሀው ነገር ተበትኗል ምኞትህ ተፈጽሞልሃል እግዚአብሔር እንደ ዓይን ብሌን አድርጎ ይጠብቅሃልና ተገዛው አመስግነው መውጣትህና መግባትህ የተባረከ ነው ሒድ ይቀናሃል።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ዘጌሠ ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ የምሥራች ተደሰት የወጣው ዘመድህ ፊቱ በርቶ ብዙ ሃብትና ጸጋ ይዞ መጣልህ።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። አንተ ሰው፤ የታመመው ቤተሰብ እስከ ፭ ቀን ብቻ ይጸናበታል እንጂ፤ ከዝያ በኋላ ይድናል አንተ ደክሞ ብታየው ትፈራለህ ነገር ግን ተግሣፁ ስለሆነ አትቸኵል ጤና ያገኛል እልሃለኁ።

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። ውጣ ተጓዝ አትፍራ ምንም ክፉ ነገር አያገኝህም። ጠላቶችህ ይፈሩሃል የምሥራች ፋልህ የቀኝ መንገድ ነው ይልሃል።

 

      ፲፮ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ግምብ። አንተ ሰው፤ ወዳጆችህ ለጥቅማቸው ሲሉ ይህችን ቤት አግባት ብለው ቢመጡብህ እኔ ደኃ ነኝና አይሆንልኝም በላቸው። ዕድለኛህ አይደለችምና ለዕድሜህ ተጠንቀቅ እልሃለኁ። መናጢ ናት ከቶ አትቅረባት።

 

 

            ፲፮ኛ ኮከብ ዓውደ ቃፍ (ቅዱስ) ክፍሉ ደቡብ።

 

      ፩ኛ፤ ለዜና መፍቀድ ትረክቦ በባሕረ ዓባይ። አንተ ሰው፤ ይህች የምትፈቅዳት ግዳጅህ የሚኣሠጋህ ነገር የላትምና ተከትላት የዘገየህ እንደሆን ታመልጥሃለች ሩጠህ ያዛት መልካም ካልሆነ በቀር ክፉ ነገር አያገኝህም ጠላትህ እንደ መንገደኛ ሐላፊ ነውና ምንም አትፍራው።

 

      ፪ኛ፤ ለነጊደ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ጣና። አንተ ሰው በዛሬው  ንግድህ ብዙ ትርፍ ታገኛለህ ዝም በል አታውራ ሒድ አስፍተህ ነገድ ሃብት ከጤና ጋር ታገኛለህ አጋጣሚ ጊዜህ ተገልጾልሃል። በምሥጢር ያዘው።

 

      ፫ኛ፤ ለበዊአ ቤት ንጉሥ በባሕረ ኳራ። አንተ ሰው፤ ምኞትህ ተፈጽሟል ወደ አሰብሀው መኰንን ቤት ፈጥነህ ግባ ከርሱ ዘንድ ደስታና ዕረፍት ታገኛለህ ክፉ ያገኘኛል ብለህ አትፍራ ነገር ግን እሙን ሁን በስራህም ሁሉ ንጉሥ ያመሰግንሃልና ተደሰት።

 

      ፬ኛ፤ ለዜና ፍትህ ትረክቦ በባሕረ ዔላ። አንተ ሰው፤ ይህ የምታስበው ፍርድ ለአንተ ይቀናሃልና ተነሥተህ ተፋረድ ታሸንፈዋለህ የሚቃውምህን ጠላት ድል ስለአደረግሀው አምላክህን በጣም አመስግነው።

 

      ፭ኛ፤ ለሠይጠ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሸኽላ። አንተ ሰው፤ ሃብት ከፈለግህ ፈጥነህ ወደ አሰብሀው ንግድ ምኞትህ በእርሱ ታገኛለህ ዛሬ ብትዘገይ ያመልጥሃልና ይህ የዛሬው ሓሳብህ ግን ፈጥነህ አድርገው። (ሽጠው)

 

      ፮ኛ፤ ለተራክቦተ ዘጌሰ ትረክቦ በባሕረ ዝዋይ። አንተ ሰው፤ ለመገናኘት ያሰብሀው ሰው አትፍራው ሒድ ተገናኘው አምላክ እንድትገናኙ ፈቅዷል ፈጥነህ ተገናኘው ኣትታክት።

 

      ፯ኛ፤ ለነጊደ ኢየሩሳሌም ትረክቦ በባሕረ አልዛዞ። ወንድሜ ሆይ፤ ኢየሩሳሌምን ከመሳለም ዝም ብለህ ታግሠህ አትቀመጥ ከዝያ ክፉዎች አታገኝም በጌታችንም በኢየሱስ ክርስቶስ መቃብር ላይ ሒደህ ብትጸልይ ዘለዓለማዊ ዋጋህን ታገኛለህ።

 

 

      ፰ኛ፤ ለዜና ደሓሪቱ ትረክቦ በባሕረ ወንጅ። አንተ ሰው፤ ለኋላ ጊዜ ተድላና ደስታ ምርኮ ከጤና ጋር ታገኛለህና የፈቀድሀውን ሳትፈራ አድርገው ጠላትህ ብላሽ ሁኖ ቀርቷል መልካም ዋጋም ከአምላክህ ትቀበላለህ።

 

      ፱ኛ፤ ለዜና ንብረት ትረክቦ በባሕረ ጎጆ-ኣም። አንተ ሰው፤ ይህ የምትፈልገው ኑሮ ያማረ ነውና አትተወው ሳይፈራ ፈጥነህ አድርገው ኑሮህ ሁሉ ይሳካልሃል ብትዘገይ ግን የኑሮን ጣዕምና ጥቅም እንደማታገኘው ዕወቅ ዛሬ እነግርሃለኁ።

 

      ፲ኛ፤ ለዜና ተሣይጦ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ዳጎ። አንተ ሰው፤ በይህ ንግድህ በፊተኛው ፈንታ እግዚአብሔር ጸጋውን ሰጥቶሃልና አትፍራ በይህ ንግድህ ተድላና ደስታ ይከብሃል ተሻምተህ ግዛው።

 

      ፲፩ኛ፤ ለደምሮ ንዋይ ትረክቦ በባሕረ ሓይቅ። አንተ ሰው፤ ገንዘብህን ለመቀላቀል ላሰብሀው ሰው እጅግ ሰነፍና ኵሩ ክፉ ቅንአት የተሞላ ነውና ገንዘብህን እንዳትቀላቅል ታገሥ ለእርሱ ባለጋራዎቹ ይመቀኙታልና ገንዘብህን ሰርቆ እንደያጠፋብህ ለብቻህ አኑር እልሃለኁ።

 

      ፲፪ኛ፤ ለዜና ፍኖት ትረክቦ በባሕረ ኄኖን። አንተ ሰው፤ ይህች መንገድህ ጤና ያላት መልካም መንገድ ናትና ፈጥነህ ሒድ በሰላም ትመለሳለህ አምላክህንም እጅግ አመስግነው።

 

      ፲፫ኛ፤ ለዜና ዘጌሠ ትረክቦ በባሕረ ሸማዝቢ። አንተ ሰው፤ ከአንተ ዘንድ ወጥቶ ወደ ሩቅ አገር የሔደው ዘመድህ በቅርብ ጊዜ ይገባልሃል። ነፍሱም ነውርና ልግም በሌለው ንጹሕ ናፍቆት ወደ አንተ መጥታ ለመገናኘትህ ትቸኵላለች።

 

      ፲፬ኛ፤ ለዜና ሕሙም ትረክቦ በባሕረ ሓዋሽ። አንተ ሰው፤ ይህ በሽተኛ ዘመድህ ነገሩ መልካም ነው ከ፪ ቀን በኋላ ደዌው ከእርሱ ይወገድለታል በኤፍራን ቀለም ጽፈህ መርበብተ ሰሎሞንን ጠልስመህ ስጠው ይድናል።

 

      ፲፭ኛ፤ ለዜና ግዒዝ ትረክቦ በባሕረ ግምብ። አንተ ሰው፤ ከአለህበት ቤት እወጣለኁ አትበል ታገሥ ምኞትህ ሁሉ በአምላክህ ፈቃድ እስኪፈጸምልህም ድረስ ምክሬን ልብ አድርገህ ስማው።

 

      ፲፮ኛ፤ ለዜና ተዋስቦ ትረክቦ በባሕረ ተከዜ። አንተ ሰው፤ ያስብሃትን ሴት ከማግባትዋ ታገሥ የታገሠ ሰው ለኋላ ከጸጸት ይድናልና ይደሰታል። በጋብቻ ነገር የረጋህ ሁን ያሰብሀው ነገርም ለሌሎች ማስደሰቻ ላንተ ግን ማሳዘኛህ እንዳይሆንብህ ተጠንቀቅ እልሃለኁ።

 

            ተፈጸመ ፍካራ ዓውደ ነገሥት አሜን።

 

 

 

 

 

                 1 ሐሳበ ጨረቃ ዘ፴ ሌሊት።

 

               አበቅቴ ሕጸጽ ቀን በ፳ ግደፍ

 

      ፩ኛ፡ ቀን ፳፯ ጨረቃ፤ መንገድ ቢሔድ ቤት ቢሠሩ ነገር ቢጀምሩ መልካም ነው። ሕልም ቢያዩም በሁለት ቀን ይደርሳል

 

 

      ፪ኛ፡ ቀን ፳፰ ጨረቃ፤ ከሚሽት ጋር በግብረ ሥጋ ቢገናኙ መልካም ነው። የሚወለደው ልጅ፤ብልሕ ዐዋቂ ጥበበኛ መርማሪ ፈላስፋ ይሆናል። ያየው ሕልም በ፯  ቀን ይፈጸማል።

 

      ፫ኛ፡ ቀን ፳፱ ጨረቃ፤ የክርስቶስ ሥዕል የተገኘበት ስለሆነ ሥዕል ቢማሩ ነገር ቢጀምሩ ለድኃ ቢዘከሩ ልጅ ቢወልዱ ይቀናል ያስመሰግናል የጠፋና የተሠወረ ነገርም ቶሎ ይገኛል ምሥጢር ይገለጻል። አምላክ ጸሎትን ይቀበላል።

 

      ፬ኛ፡ ቀን ፴ ጨረቃ፤ መጥፎ ነው ተጠንቀቅ ነቅተህ ጸልይ። አደገኛና የደም ቀን ነው።

 

      ፭ኛ፡ ቀን ፩ ጨረቃ፤ መንገድ ቢሔዱ ቢሸጡ ቢለውጡ ጥሪት ቢያስቀምጡ መታሰቢያ ቢያደርጉ ሐውልት ቢቀርፁ ቤት ቢመሠርቱ ውል ቢዋዋሉ ቃል ኪዳን ቢገቡ ይሆናል የጠፋ ነገርም ሁሉ ይገኛል። ኖኅ በመርከብ የተሳፈረበት ቀን ስለሆነ ከአደጋ ከወራሪ የተሸሸገ ነገር ሁሉ ይድናል።

 

      ፮ኛ፡ ቀን ፪ ጨረቃ፤ ክርስቶስ ያስተማረበት ስለሆነ ሕፃን ፊደል ቢጀምር ሊቅ መርማሪ ተርጓሚ ብሉይና ሐዲስ ዓዋቂ ታሪክ አስተካካይና ልበ ብሩህ ይሆናል። በዚህ ሌሊት የሚወለደው ግን ታሪክ አጥፊ ሌባ ቀማኛ ወምበዴ አመዝባሪ ሽፍታ ጋለሞታ ይሆናል። ነገር ግን በዚህ ሌሊት ደግሞ ምግባርና ቢያሣምሩና ቢጸልዩ ይሠምራል ሕልምና የጠፋ ነገርም ሁሉ በቶሎ ይገኛል።

 

      ፯ኛ፡ ቀን ፫ ጨረቃ፤ ቢሸጡ ቢለውጡ ሀብት ይነሣበታል የሸሸ ይያዝበታል የጠፋ ይገኝበታል ቢያስታርቁበት ይሠምራል። በደለኛ ተጸጽቶ ንስሓ ይገባበታል።

 

      ፰ኛ፡ ቀን ፬ ጨረቃ፤ ዘር ቢዘሩ አትክልት ቢተክሉ መልካም ይሆናል ሕልምና የጠፋ ነገርም በ፲፪ ቀን ይገኛል ነገር ግን የሚወለደው ይሞታል ዕድሜው ያጥራል።

 

      ፱ኛ፡ ቀን ፭ ጨረቃ፤ ሐዋርያት ክርስቶስን እጅ የነሡበት ነው። ይህን ጊዜ የሚወለደው የመኳንንትና የመሳፍንት ባለሟላ ይሆናል የተጣለና የተካሰሰ ባለ ዕዳው ይታገሠዋል ሕልሙ ግን ግብዝ ነው።

 

      ፲ኛ፡  ቀን ፮ ጨረቃ የሚወለደው ሃይማኖታዊ ምግባረ መልካም ይሆናል ዕለቱ ግን የኃዘን ዕለት ።

 

      ፲፩ኛ፡ ቀን ፯ ጨረቃ፤ ይሁዳ ክርስቶስን ለ፴ መክሊት የአሳለፈበት ስለሆነ አሽከርና ሎሌ ጌታቸውን ለባላገራው አሳልፈው ይሰጡበታል። ምግባረ ሥጋ ቢያደጉ ልጅ ቢድሩ መልካም ነው የጠፋና የሸሸም ይገኝበታል።

 

      ፲፪ኛ፡ ቀን ፰ ጨረቃ፤ የታመመና የሚወለድ ያንቀላፋል (ይሞታል) የሚጠፋም ነገር ሁሉ ይጠፋል ራሱን የሚላጭ መከራ ይሰፍርበታል ሕልሙም ግብዝ ነው።

 

      ፲፫ኛ፡ ቀን ፱ ጨረቃ፤ እህልና ውሃ አይገናኝም

 

      ፲፬ኛ፡ ቀን ፲ ጨረቃ፤ አዳም የተፈጠረበት ሄሮድስ ሕፃናትን የአስፈጀበት ሳጥናኤልም ከመዓርጉ የወደቀበት ስለሆነ ያልታሰበ ነገር ይገኝበታል (ይታይበታል) ንጹሕ ሰው አለ ኃጢአቱ በፍርድ ያልፍበታል። የባለ ሥልጣን ትእዛዝ ይጸናል ገበነኛ ወደ ግዞት ቤት ያልፍበታል። እግዚአብሔር የየዋሃን ጸሎት ይሰማበታል ሰው ማልዶ አይውጣ ከፈረስና ከመንኰራኵር ላይ ከአለህ ተጠንቀቅ ከሴት ንጹሕ ሁን አትድረስባት ሕልሙ ግንግብዝ ነው።

 

      ፲፭ኛ፡ ቀን ፲፩ ጨረቃ፤ አዲስ ነገር ቢጀምሩ መንገድ ቢሔዱ መሠረት ቢጥሉ መልካም ነው ጸሎትና ምጽዋት ቢያደርጉ ይሠምራል። ሕልሙ ግን አይረባም እንደ ቅጀት ነው።

 

      ፲፮ኛ፡ ቀን ፲፪ ጨረቃ፤ ክርስቶስ ሐዋርያትን የአስተማረበት ነው የታመመ ያንቀላፋበታል የሔዱበትና ያሰቡት ነገር ሁሉ ፍጹም ይሆናል ይከናወናል የተበደለ ይካሣል ሕልሙም ዕለቱን ይደርሳል። የሚወለደውም ሰማዕት ሃይማኖተኛ ጥቡዕ ሐዋርያ ይሆናል።

 

      ፲፯ኛ፡ ቀን ፲፫ ጨረቃ፤ ክርስቶስ በገሃነመ እሳት የሚኖሩትን ሰዎች የጎበኘበት ነው በዚህ ሌሊት የሸጠና የለወጠ ይከስራል የሸሸና ያመለጠ ይያዛል የሚወለደውም ድዳ አፈ ኮልታፋ ይሆናል ሕልሙ ግን ግብዝ ነው።

 

      ፲፰ኛ፡ ቀን ፲፬ ጨረቃ፤ ዘር ቢዘሩ አትክልት ቢተክሉ ከሴት ቢገናኙ ቢሸጡ ቢለውጡ ይቀናል ያልታሰበ ደስታ ይገኝበታል ሕልሙም ጭምር መልካም ነው።

 

      ፲፱ነኛ፡ ቀን ፲፭ ጨረቃ፤ እግዚአብሔር ፲ቱ ቃላተ ኦሪትን ይዞ በደብረ ሲና ከሙሴ ጋር የተገናኘበት ነው ሕፃን ከትምህርት ቤት ቢያገቡትና ጽሕፈትም ቢያስተምሩበት መልካም ነው መንገድ ቢሔዱ ግን መጥፎ ነው አይቀናም አደጋ አለውና በጸሎት ይመለሳል። የሚወለደው ያንቀላፋል ሕልሙ ግን በቶሎ ይደርሳል ይፈጸማል።

 

      ፳ኛ፡ ቀን ፲፮ ጨረቃ፤ እግዚአብሔር አብርሃምን ጠርቶ የተገናኘበት ቀን ነው በዚህ ዕለት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ሀብትና ጤና ጽድቅና ደስታ ይገኝበታል ሠርግ ቢያደርጉ ከሰው ጋር ቢተዋወቁ ነገር ቢቋረጡ ውል ቢዋዋሉ መልካም ነው የሚወለደውም ልጅ ጥበበኛ ሊቅ ፈላስፋ ይሆናል መድኃኒት ቢያደርጉ ይሠምራል ድውይ ይፈወስበታል የጠፋም ከመንገድ ይገኛል ሕልሙ ግን ግብዝ ነው።

 

      ፳፩ኛ፡ ቀን ፲፯ ጨረቃ፤ ወንጌላዊ ማርቆስ የተወለደበት ነው በዚህ ዕለት የሚወለደው ደፋርና ልበ ጽኑ ነው ለቤተ መንግሥት ለመሳፍንትና ለመኳንንት ጠንካራ ጽኑ ቢትወደድ ይሆናል። የታመመ ፈውስ ያገኛል ሕልሙም ዕለቱን ይደርሳል። የሃይማኖት ሥራም ይከናወንበታል የጣዖት ቤት ይፈርስበታል። የተሟገተ ይረታበታል ጠላት ይጐዳበታል።

 

      ፳፪ኛ፡ ቀን ፲፰ ጨረቃ፤ የእንግዚአብሔር ቸርነትና ምሕረት ይገኝበታል የሸጠ የለወጠ የተቀበለ ይባረክለታል በዚህ ዕለት የሚወለደው ግን ጨካኝ ክፉ አመዝባሪ መጥፎ መሠሪ ሌባ ወምበዴ ምቀኛና ቂመኛ ይሆናል። ሕልሙ ግን የታመነ ነው።

 

      ፳፫ኛ፡ ቀን ፲፱ ጨረቃ፤ ዮሐንስ መጥምቅ የተወለደበት ነው በዚህ ዕለት የሚወለደው ደፋር ጀግና አስተዋይ ንጹሕ ታሪከና ይሆናል። መንገድ ቢሔዱ ቢሸጡና ቢለውጡ ቢቀበሉና ቢሰጡ ይባረካል የሚወለደው ዕድሜው አጭር ይሆናል። ሕልሙ ግን ግብዝ ነው።

 

      ፳፬ኛ፡ ቀን ፳ ጨረቃ፤ ክርስቶስ በዘባነ አድር ተቀምጦ ወደ ቤተ መቅደስ የገባበት ነው። መንገድ ቢሔዱ ቢዘሩ ቢተክሉ ግብረ ሥጋም ቢያደጉ ለፍሬ ይሆናል። ቢነግዱና አደራ ቢሰጡ ግን ይከስራል።

 

      ፳፭ኛ፡ ቀን ፳፩ ጨረቃ፤ ጎግ ማጎግ ሐሳዌ መሲሕ የተወለደበት ነው በዚህ ሌሊት የሚወለደው ረዢም ቁመት ገፋፋ ልብሰ ዘርፋፋ አገርዣ ንፋ ግዙፍ ነገረ ጐልዳፋ ልብሰ አዳፋ አስቀያሚ ሞኛ ሞኝ ውስጠ ብልሕ ሲያውቅ ተበላጭና ተታልሎ አታላይ ይሆናል። መንገድ ቢሔዱ አይቀናም ምግባር ቢሠሩ እንግዳ ቢቀበሉ ለድኃ ቢሰጡ የተጣላ ቢያስታርቁ ኃጢአት ይሰረያል።

 

      ፳፮ኛ፡ ቀን ፳፪ ጨረቃ፤ መንገድ ቢሔዱ ማናቸውንም ነገር ቢሉና ቢጀምሩ ያሰቡትንም ሁሉ ቢሠሩ ሁሉም ፍፁም ይሆናል። ሕልሙ ግን ቅጀት ነው አይረባም።

 

      ፳፯ኛ፡ ቀን ፳፫ ጨረቃ፤ አብርሃም ይስሐቅን መሥዋዕት ያቀረበበት ነው። ኃጢአተኛ ቢናዘዝ ኃጢአቱ ይሰረይለታል ለድኃ የመጸወተ በሽተኛና እስረኛ የጎበኘ የተጣላ ያስታረቀ ከመሥዋዕት የበለጠ ይቈጠርለታል። ሕልሙ ግን ግብዝ ሃኬተኛ ነው።

 

      ፳፰ኛ፡ ቀን ፳፬ ጨረቃ፤ ሰሎሞን ቢመጸውት ሰይጣን መርዝ ነዛበት ነገር ግን እግዚአብሔር ባረከው ከዳኛ ፊት አትቅረብ ይጠምሃል የሚያገባ መልካም ንብረት ይሆንለታል የሚወልደውም ይባረክለታ።

 

      ፳፱ነኛ፡ ቀን ፳፭ ጨረቃ፤ የሚሸጥ የሚለውጥ ቤት የሚሠራ ይፈጸምለታል የሚወለደውም የንጉሠ ነገሥት ቢትወደድና ባለሟል  ይሆናል ሕልሙም እሙን ነው።

 

      ፴ኛ፡ ቀን ፳፮ ጨረቃ፤ ተጠንቀቅ መንገድ አትሒድ ጠንቀኛ ዕለት ነው ግርግርና ሽብር ድንገተኛ አደጋ ይሆናል። እርጉዝ በድንጋጤ ያስወርዳታል የታመመ በድንጋጤ ይፈወሳል ዓመጸኛ ያዝዝበታል የኮበለለ ግን ይያዝበታል እስረኛ ይፈታበታል ሕልም ያየም ይፈጸምለታል በዚህ ዕለት ያልታሰበ ሰው ለትልቅ መዓርግ ይመረጣል። ሕልሙ ግን አጉል ወላዋይ ነው።

 

                       2     

                  ሐሳበ ሕልም።

 

        ስም ቀን ወርኁንና ወንጌላዊውን በ፰ ግደፍ።

 

      ፩፡ሲወጣ ሄኖክ፤ መልካም የሆነ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ያለበት ሕልም ታልማለህ እርሱም በፍጥነት በገሃድ ይፈጸምልሃል።

 

      ፪፡ ያዕቆብ፤ መልካም ሕልም ሀብትና ሢሣይ ከዕድሜ ጋር የማይጠፋ የማያልቅ የማይደቅ ለትውልድ የሚተርፍ የእግዚአብሔር ቸርነት የማይለየው ታልማለህ።

 

      ፫፡ ዮሴፍ፤ ከብዙ ፈተና በኋላ ሙሉ ሰው ስትሆን ደርሶ ለወገንህ ትምክሕት ትሆናለህ ምሥጢራዊ ሕልም ታልማለህና ጊዜው ሲደርስ ትከብርበታለህ በዚሁም ሕልምህ ዓዋቂና ተርጓሚ ትሆናለህ ትርጓሜህም ውሎ ሳያድር ይደርሳልና እንደ ትንቢት ይፈጸማል።

 

      ፬፡ ፈርዖን፤ ክፉና መልካም የሆነ ልትተረጕመው የማትችል በመንግሥትና በሀገር ላይ የሚደርስ ብርቱ ትርጓሜ የሚያስፈልገው ሕልም ታልማለህ።

 

      ፭፡ ናቡከደነፆር፤ በገሃድ አይተኸው እንደገና የሚጠፋብህ ሕልም ታልማለህ። ነገር ግን ሌላ ሰው እንደገና በራእይ ተገልጾለት ሲፈታው ትሰማለህ።

 

      ፮፡ ዳንኤል፤ በጾምና በጸሎት በኀዘንና በትካዜ ለመናፍቅ የተገለጸለት ሕልም ላንተም ተገልጾልህ ታያለህ ይህም ወዲያው ይፈጸማል በዚህ ምክንያትም አንተ ከብረህ አምላክህን ታከብርበታለህ።

 

      ፯፡ ዠረደሸት፤ (ሰብአ ሰገል) ደግ ነገር የሆነ እሙን ሕልም ታልማለህ በዚሁም ሕልም ተደንቀህ እንዳይረሳ ለመጭው ትውልድ ጥቅም እንዲሆን በማስታወሻ ጽፈሕ ትተወዋለህ ነገር ግን አንተ አልፈህ በመጭው ትውልድ ይፈጸማል።

 

      ፰፡ ዮሐንስ ራእይ፤ በሕልም በራእይ በገሃድ ግሩም የሆነ ሰማያዊ ምሥጢራት ታልማለህ በግዞት ቤት ሁነህም እየደጋገምህ ታየዋለህ ነገር ግን አንተ ሳትደርስበትና ሳታየው ታንቀላፋለህ (ትሞታለህ) ይኸውም ለመጭው ትውልድ እንደ ትእዛዝና ትዝብት ሆኖ ይፈጸምባቸዋል ነገር ግን አንተ ከቅዱሳን ሁሉ የተመረጥህ ነው።

 

                        3

                   ሐሳበ ሐራ ዘመን።

 

ስምና የእናትን ስም ወንጌላዊውና ዓ.ም በ፱ ግደፍ።

 

      ፩፡ ሲወጣ፤ መልካም ነው ሀብትና ሹመት ያገኛል ምቀኛውም ያሸንፋል በጥቅምትና በየካቲት ፲፭ኛ ቀን ይጠንቀቅ።

 

      ፪፡ ወላዋይ ነው በቤትህ ሕመምተኛ እንዳለ ተጠንቀቅ ሕፃን ይሞትብሃል አንተ ግን ኃይልና ሞገስ ታገኛለህ ታሸንፋለህ ከቀይ ሰው ተጠንቀቅ በጥቅምትና በመጋቢት እስከ ፲፭ኛ ቀን ይጠንቀቅ።

 

      ፫፡ መጥፎ ነው፤ ራስህን ለካህን አሳይ ንስሓ ግባ የመቃብር ልብስህን አሰናዳ ድንገተኛ ሞት ያስፈራሃል በጥቅምትና በግንቦት በሐምሌ እስከ ፲ኛ ቀን ተጠንቀቅ።

 

      ፬፡ ወላዋይ ነው ሕፃን ይሞትበታል ገንዘብ ይጠፋበታል እሳትና ተስቦ ያስፈራዋል ይጸልይ ስለገንዘቡ ያዘነ እንደሆነ ግን ሕይወቱን በገዛ እጁ ያጠፋል በታኅሣሥና በመጋቢት እስከ ፲፭ኛ ቀን ይጠንቀቅ።

 

      ፭፡ መልካም ነው፤ ሹመትና ደስታ ያገኛል ምቀኛውን ያሸንፋል ማልዶ አይወጣ ወደ አስክሬን አይቅረብ ሟርትና ደንቃራ ያስፈራዋል በጥቅምትና በኅዳር በግንቦት እስከ ፲፪ኛ ቀን ድረስ ይጠንቀቅ።

 

      ፮፡ መጥፎ ነው፤ ከ፫ኛው ቁጥር ጋር ልዩነት የለውም እንዲያውም በነሐሴ ፳ ቀን መቃብሩን ያዘጋጅ በታኅሣሥና በነሐሴ በሚያዝያ እስከ ፳፬ኛ ቀን ድረስ ይጠንቀቅ።

 

      ፯፡ መልካም ነው፤ ዕድሉ ለሃብትና ለሹመት ይገፋፋዋል ጠላቱ ይወድቅለታል የነገሥታትና የመኳንንት ፍቅር ይሆንለታል ያሰበው ሁሉ ይቀናዋል በጥቅምትና በኅዳር በመጋቢትም እስከ ፲፮ኛ ቀን ይጠንቀቅ።

 

      ፰፡ ወላዋይ ነው፤ ኃዘን ያገኘዋል ከቤተሰቡ ጋር ይጣላል ገንዘብ ይጠፋበታል በጣም ያዘነ እንደሆነ በራሱ ላይ ሞት ያስፈራዋል በመጋቢትና በሐምሌ እስከ ፲፯ ቀን ይጠንቀቅ።

 

      ፱፡ መልካም ነው፤ ሹመት ያገኛል ነጋሪት ያስመታል ምቀኛውን ያጠቃል ቢታመም ይድናል የሆድ በሽታ ያስፈራዋል ወደ በሽተኛ ቤት አይሒድ በሚያዚያና በሰኔ በነሐሴ እስከ ፳፩ኛ ቀን ድረስ ይጠንቀቅ።

 

 

                              4    

 

                        ሐሳበ ወርኅ

 

ስምና የእናት ስም ወንጌላዊውና ወርኁን በ፲፪ ግደፍ።

     

      ፩፡ሲወጣ ጥቂት ገንዘብ ታገኝና ታጣለህ ሌባና የሰው ዓይን ያስፈራሃል ሴት ጋር ትጋጫለህ እስከ ፲፪ ቀን ድረስ ተጠንቀቅ።

     

      ፪፡ መልካም ነው ምቀኛህ ይወድቅልሃል ነገር ግን ጥቂት የሆድ በሽታና ትካዜ ያገኝሃል እስከ ፳፩ ቀን ድረስ ተጠንቀቅ።

     

      ፫፡ መጥፎ ነው፤ ሞት ያስፈራሃል ምቀኛ ይነሣብሃል እስከ ፲፯ ቀን ተጠንቀቅ።

     

      ፬፡ መልካም ነው ሙሉ ደስታና የተሠወረ ገንዘብ ታገኛለህ ወንዝ አትሻገር ጐርፍ ያስፈራሃል አንተና ከብቶችህ ትታመማላችሁ ገንዘብ ይጠፋብሃል ጠላትም ይነሣብሃልና እስከ ፲፮ ቀን ተጠንቀቅ።

     

      ፭፡ ክፉ ነው ከነምልክቱ በጐረቤትህ ልቅሶ ትሰማለህ የሚያሳዝን ወሬ ታገኛለህ መድኃኒት አትጠጣ ሞት ያስፈራሃል ከጌታ ቤት አትራቅ ደጅ ጥናትም ይሠምርልሃል ነገር ግን እስከ ፲፭ ቀን ተጠንቀቅ።

     

      ፮፡ ክፉ ነው ባለጋራና ምቀኛ ክፉ ነገር ይመክርብሃል ደምና ደንቃራ ያስፈራሃል በሌሊትና በጨለማ ከቤትህ አትውጣ ጋኔል ይፃረርሃል ከጥቁር ሴት ጋር አትገናኝ ገንዘብ ይጠፋብሃል ቀይ በግ ወይም ቀይ ዶሮ ጭዳ በል እስከ ፲፬ ቀን ተጠንቀቅ።    

 

      ፯፡ ወላዋይ ነው ደስታና ኃዘን ትሰማለህ በጽኑ ደዌ ትያዛለህ እንዲምርህ ፈጣሪህን ለምን ገበያ ይሠምርልሃል ጉሮሮህን ያምሃል ገንዘብህም ሴት ትወስድብሃለች ነጭ ነገር ደም አፍሥ እስከ ፲፯ ቀን ድረስም ተጠንቀቅ።

     

      ፰፡ ደምና ጥቁር ሰው ያስፈራሃል ራስህንም ትታመማለህ በቀትር ትለከፋለህ ቀይ በግ ወይም ዶሮ በፍጥነት ጭዳ በል ምቀኛህንም ትጥለዋለህ ነገር ግን እስከ ፲፯ ቀን ተጠንቀቅ።

     

      ፱፡ እጅግ መልካም ነው ደስታና ሲሳይ ታገኛለህ ትሾማለህ ትሸለማለህ ከጌታ ቤት አትራቅ መንገድ ብትወጣ ቀንቶህ ትገባለህ ነገር ግን ከፈረስ ወይም ከበቅሎ ላይ እንዳትወድቅ እስከ ፲፭ ቀን ተጠንቀቅ።

 

      ፲፡ ደምና እሳት ያስፈራሃል ከሴት ጋር ትጋጫለህ ወደ ሩቅ ቦታ አትሒድ ገንዘብ ይያዝብሃል ትታመማለህ የጥቁር ገብስማ ዶሮ ጭዳ በል እስከ ፲፱ ቀንም ተጠንቀቅ።

 

      ፲፩፡ የጠፋብህን ገንዘብ ታገኘዋለህ ከባለጋራህም ጋር ትታረቃለህ እስከ ፳፩ ቀን ድረስ ተጠንቀቅ።

 

      ፲፪፡ ዘመድና አዝማድ ምቀኛና ባለጋራ ክፉ ነገር ይመክሩብሃል ከጐረቤትህ መጠጥ አትጠጣ መድኃኒት ያስፈራሃል እስከ ፲፫ ቀን ድረስ ተጠንቀቅህ ጸልይ።

                        5

 

                 ሐሳበ ባሕርይ ወመነጽር።

     

      ስምንና የእናትን ስም ወንጌላዊውንና ወርኁን በ፯ ግደፍ።

 

      ፩፡ ሲወጣ በእሑድ ቀን ተረገዘ፤ በሌጌዎን ይመሰላል መልኩ ጠይም በልቶ የማይጠግብ ፊተ ሰፊ ጆሮው ከሩቅ የሚሰማ ሌባ አቀናዳቢ (አቀናባሊ) እሠራለሁ ባይ ዕቡይና ኵሩ ነፍሰ ገዳይ ያውም አባቱን ነው በክፉ ጊዜ በመንፈቀ ሌሊት ተረገዘ ወደ ጠላቱ አገር ይሔዳል ኮረብታና ነፋሻ ስፍራ ይሆነዋል።

 

      ፪፡ በሰኞ ቀን ተረገዘ፤ በፀሐይ ይመሰላል ገጸ ፀሐይ ነው ሢመት ያገኛል ዓይነ ሌባ ልበ ጐልማሳ ቂመኛ ባለ ሥራይ ነው ዘመዱን አውስቦ ይወልዳል ሀብቱ እንዳይጠፋበት ሰኞ ቀን የትም አይሒድ ከቤት ይዋል ሮብ ቀን ሞት ያስፈራዋል።

 

      ፫፡ ማክሰኞ ተረገዘ፤ በውሃ ይመሰላል ገጹ ጥቁር ሀብተ ጸሊም ዕቡይ ነው ብልቱን መጨበጥና አውስቦ ማዘውተርን ይወዳል ውሃም አብዝቶ ይጠጣል ከሰው ጋር መንገድ መሔድና ቀጠሮ ማብዛትን ይወዳል በዕለተ ሐሙስ በነግህ ያወስባል ቅቡዕና ባሕታዊ ይወልዳል በሩካቤ ጊዜ እግዚአብሔርንአይፈራም ካገኘው ጋር ይጋደማል።

 

      ፬፡ ሮብ ተረገዘ፤ ክፉ ነው በአራዊት ምድር ይመሰላል ዓይኑ ጥፉ ጆሮው የማያዳምጥ ፊቱ ደም የሚመስል ልበ ጐምዛዛ ይሆናል እርሻና የከብት ርቢ ይሠምርለታል የሚወልደው ልጅም እንደ እርሱ ንፉግ እኩይና አሉተኛ መሳይ ይሆናል። በቀትር በፌራና በምች ይሞታል አባትና እናቱ ይወርሱታል።

 

      ፭፡ ሐሙስ ተረገዘ፤ መልካም ነው አርአያው ደኅና ሰው ይመስላል ሐቀኛ ነው ዕቡይና ዓመል ተመልካች ጠበኛ ምግባር ይሆናል ጋኔን ይፃረረዋል ድምፁ ክቡር ቃሉ እውነተኛ ጸሎቱ ሥሙር ምሉአ ምግባር ነው ከአምላኩ ጋር ይመሳሰላል በቀትርና በሰርክ የሰው ዓይን ያስፈራዋል በቅዳሜ ቀን ይወልዳል እርሻ ፈረስ በቅሎ ይሠምርለታል።

 

      ፮፡ ዓርብ ተረገዘ፤ ሀብተ መብረቅ ውሥጠ ልቡ ቅምር ነው ሣቅ ያበዛል ቅንዝረኛና ኩራተኛ ነው በ፬ቱ ጠባያተ ፍጥረት ይመሰላል ገጸ ማኅተምዕዝነ ሰሚዕ ልበ ጥቡዕ እግረ ርቱዕ ይሆናል። የዋህ ይመስላል ምሥጢሩ ጥልቅ ይሆናል በ፵ ዘመኑ ሥራይ ያስፈራዋል ጻድቅ ተነሣሒ ይሆናል በሥራይ ሞት ያስፈራዋል ከብት ይጠፋዋል ግርፋት ያገኘዋል ብዙ ሴት ያገባል እርሻ ይሆንለታል ከዳተኛ ነው ብዙ ዘመቻ ይዘምታል የሰው አዳኝ ያስፈራዋል ሀብቱ ብዙ ነው ኮረብታ ሥፍራ ይሆነዋል ዓርብ ተረግዞ እሁድ ይወለዳል።

 

      ፯፡ በቀዳሚት ተረገዘ፤ እግረ መዓት ሞገደ መዓት አለው ጆሮው ከሩቅ ይሰማል ዋሾ ሴረኛ እሺ ብሎ ከዳተኛ ነው አህያ ርኵስ ከብት ይሆንለታል የጀርባ ደዌ አለው መብል ይወዳል ብልቱ ይቆማል ነገር ያመላልሳል ሀብቱ እውነተኛ አይደለም ያልቅበታል በራሱ ቀላጅ ይመስላል ነገር ግን ጸሎተኛ ነው በእኩለ ቀን ወይም በሠርክ የጥላ ወጊ ውጊያ ያስፈራዋል ወደ ጠላቱ አገር አይሒድ የድንገት ሞት ያስፈራዋል።

 

 

                         6 ሓሳበ ጠባይ

 

 

      ስምን ብቻ በ፱ ግደፍ ፩፤ ሲወጣ ግሰላ ነው፤ ዓይነ ፈሪ ንፉግ ካልነኩት አይነካ ሰው አይወድ ነው። ፪፤ ውሻ ነው፤ የማይከብር የማይሾም ወራዳ ሀብቱ ትንሽ የማይቀመጥ ዘዋሪ ነው ። ፫፤ ድመት ነው፤ ሁሉ ሰው የሚወደው የሚሄድበት የማይታወቅ ሴሰኛና ቅንዝረኛ ተለማማጭ ሁሉን መስሎ አዳሪ ከዳተኛና ዋሾ ተታላይ ከተመቸው ቀሪ ነው። ብቸኝነትን ይወዳል አሳዛኝ መሳይ ነው። ፬ ፤ ተኵላ ነው፤ለማኝ ያየውን ሁሉ ከጃይ ዘዋሪ ከተመቸው ሁሉ ሂያጅ መብልና መጠጥ ወዳጅ ከአንድ ቦታ የማይቀመጥ ኮብላይና መለኛ ነው። ፭፤ ጅብ ነው፤ ጉልበታም ልበ ፈሪ ከተነሣ የማይወድቅ ከተሾመ የማይሻር ጠላቱን አሸናፊ መቸም መች መብልና መጠጥ የማያጣ ጉረኛ ነው። ፮፤ ነብር ነው፤ ዓይነ ደፋር ደረቅ ኵራተኛ ዕቡይ ጠላቱ ሁሉ አሸናፊ ሆዱ የሚባባ ከተነሣ የማይወድቅ ከተሾመ የማይሻር ንጹሕና ጸሎተኛ ነው። ፯፤ አንበሳ ነው፤ ክፉ አመጸኛ ዕቡይ ኩራተኛ ከወደቀበት የማይነሣ ነው ናቂ ሀብቱን በገዛ እጁ አሳጣሪ ነው። ፰፤ ዝሆን ነው፤ ሞኝ መሳይ ዝግተኛ ያለብርቱ ነገር የማይወድቅ ኃይለኛ ቂም ያዢ ወዳጁንና ጠላቱን የማይለይ ከያዘ የማይለቅ ከተሾመ የማይሻር ዕድሉ ሁልጊዜ ዘመቻ ነው። ፱፤ ድብ ነው፤ ይሉኝታ የሌለው ዘማዊ ቅንዝረኛና ዋሾ የነገር መልስ ዐዋቂ አሉተኛ ሲናገር እውነትነት አስመስሎ ሁሉን የሚያሸንፍ ነው።

                              7

                         ሓሳበ ረዋዲ (ጠላት)

 

      ስምን ብቻ በ፱፤ ግደፍ። ፩፤ ሲወጣ ቀበሮ ነው፤ አዳኝ ከአደጋ ተሠዋሪ ሀብታም ነው። ፪፤ ጥንቸል ነው፤ አሳዘኝ ተመስዋች ወራዳ ነው። ፬፤ ተኵላ ነው፤ ደፋርና አዳኝ ኃይለኛ ሀብታም ተንኮለኛና መለኛ ነው ዕድሜአማ ለጠላቱ የማይጠመድ ዕድለኛ ነው። ፭፤ ጅብ ነው፤ ልበ ፈሪ ጉልበታምና ሲሳያም ድምፀ ጀግና ነው። ፮፤ ነብር ነው ፤የእግዚአብሔር ወዳጅ ንጹሕ ጸሎተኛ ፍርድ ዐዋቂ ሀብታም ጦም የማያድር ንፉግና ጠርጣሪ ኩሩ አክብሩኝ ተለማመጡኝ ባይ እልከኛ ነው። ፯፤ አንበሳ ነው፤ ኃይለኛ አዳኝ ኩሩ አስደንጋጭና አስፈሪ ፎካሪ ጭንቀታም ኩርፍተኛና ታማኝ ሀብታምና ሲሳያም ዕድለኛ ከአለበት የሚገኝ ሰው ናቂ ቅልጥሙ አማኝ ነው። ፰፤ ዝሆን ነው ዝምተኛ የዋህ መሳይ ቂመኛ ሰውነተ ግዙፍ ዕድሜአማና ሀብታም ቸርናከሰው አዳሪ ሳይነኩት አይነካ ነው። ፱ ድብ ነው፤ አዘንጊ ልበ ቢስ ሁሉን ናቂ ቅንዝረኛና ዝምተኛ ሀብታምና ለጋስ ነው።

 

            8 ሓሳበ መከራ ስምና ወርኁን በ፱ ግደፍ።

 

      ፩፤፪፤ ሲወጣ ሠናይ ወርኀ በኵሉ። ፫ እኪት ሞት ወኃዘን ይመጽእ ብከ። ፬፤ ወላዋይ ነው በዘመኑ የኃዝን ንዋይ ይጠፍአከ ኢኮነ ሠናይ ወእኵይ ። ፭፤ ሠናይ ውእቱ ሑር ኀበ ነገሥት ወመኳንንት። ፮፤ እኩይ ኃዘን ወመከራ ይመጽእ ብከ። ፯፤ ሠናይ ወርኅ በኵሉ። ፰፤ እኩይ ሑከት ወኃዘን ይመጽእ ብከ ተዓቀብ። ፱ እኩይ ዝብጠት ወሞቅሕ ስደት ወመከራ ይመጽእ ብከ ተዓቀብ ወጸሊ።

 

                              9

           ሓሳበ ሥቃይ። ስምና ወርኀ ወንጌላዊውንም በ፭ ግደፍ።

 

      ፩፤ ሲወጣ ክፉ መከራ ይመጣብሃል መድኃኔ ዓለምን ዘክር። ፪፤ ፍሥሐ ወሐሤት ትረክብ ፀረከኒ ትመውእ። ፫፤ እኩይ ውእቱ ኢትሑር በፍኖት ደም ይተልወከ ጊዜ ሞትከ ውእቱ። ለሚካኤል ተሳልና ጸልይ ነጭ በግ እረድ ። ፬፤ ጠላት ይነሣብሃል ነገር ግን አንተ ታሸንፈዋለህ የምትወደው ይታመምብሃል እንደ ጨለማ የከበደ ነገር ያገኝሀል። ፭፤ መንገድ ትሄዳለህ ጠላትህን ታሸንፋለህ የአሰብከው ነገር ይከናወንልሃል በዚሁ ለገብርኤል ተሳል።

 

      ፩፤ ሲወጣ በጥቅምት ወይም በመጋቢት ቁራኛ ምቀኛ ከሳሽ ይነሣብሀል ተጠንቀቅ። ፪፤ በመስከረምና በየካቲት ግንቦት ቤተ ሰዎችህን ታጠፋለህ በበረሀ ገንዘብ ይጠፋብሀል ብርቱ ኃዘን ያገኝሃል። ፫፤ በታኅሣሥና ሰኔ በሽታ ብድብድ ያገኝሃል በቀይ ሴት ጥል ያስፈራሃል በደም ትሞታለህ በሰኔ ተጠንቀቅ። ፬፤ በጥርና መጋቢት ቀሳጢ ወስላታ ያጠቃሃል ገንዘብ ይጠፋሃል ኃዘን በሽታ ያገኝሃል አጋንንት ይጠናወቱሃል ተጠንቀቅ። ፭፤ በመጋቢትና ሐምሌ መሳፍንት ይክዱሃል ያሳጡሃል ድንገት ትታመማለህ እስከ ፷ ቀን ድረስ ተጠንቀቅ።፯፤ በሚያዝያና ሰኔ የሆድና የራስ ምች ተስቦ ወይም የዛር ውላጅ ያገኝሃል ገንዘብ ይጠፋብሃል የሴት ሥራይ ያስፈራሃልና ተጠንቀቅ።፯፤ በጥርና ግንቦት ከሳሽ ይነሣብሃል ግዝትና መሓላ ያስፈራሃል ሚስትህ ነገር ታነሣብሃለች አንተም ትታመማለህ። ፷፤ በየካቲትና ሰኔ በትንሽ ነገር ወንድምህ ወይም ጎረቤትህ ያሳዝንሃል። ፱፤ በመስከረም ወይም በጥቅምት መንገድ አትሂድ አይቀናህም ድህነት ያገኝሃል ምቀኛ ይነሣብሃል። ተጠንቅቀህና ነቅተህ ጸልይ።

 

 

                  10 ሓሳብ ልደት

 

      ስምን የእናትና የአባትንም ስም በ፯ ግደፍ። ፩፤ ሲወጣ ጥንተ እሑድ በጥንተ ዕለት እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን በፈጠረበት ቀን እንድትወለድ ፈቃዱ ሆነ። ፪፤ በጥንተ ጠፈር ጥንተ ሰኑይ እግዚአብሔር ጠፈርን በፈጠረበት ቀን እንድትወለድ ፈቃዱ ሆነ። ፫፤ በጥንተ ቀመር ጥንተ ሠሉስ እግዚአብሔር አትክልትን በፈጠረበት ቀን እንድትወለድ ፈቃዱ ሆነ። ፬፤ በጥንተ ዮን ጥንተ ረቡዕ እግዚአብሔር ፀሐይና ጨረቃን ከዋክብትንም በፈጠረበት ቀን እንድትወለድ ፈቃዱ ሆነ።፭፤ ጥንተ ሐሙስ በጥንተ ተሐዋስያን እግዚአብሔር ዓሣዎችንና አዕዋፍን የባሕርንም እንሳሳ ሁሉ በፈጠረበት ቀን እንድትወለድ ፈቃዱ ሆነ። ፮፤ ጥንተ ዓርብ በጥንተ ሰብእ እግዚአብሔር እንስሳንና አራዊትን ሁሉ ሰውንም በአርኣያው በፈጠረበት ቀን እንድትወለድ ፈቃዱ ሆነ። ፯፤ ጥንተ (ሳብዒት) ሰንበት በጥንተ ቀዳሚት እግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና ፳፪ቱን ሥነ ፍጥረት ከፈጠረ በኋላ በዕረፍት ቀን እንድትወለድ ፈቃዱ ሆነ።

 

                           11

 

                    ሓሳበ አድባር።

 

      ስምና የሚስትን ስም የቦታውንም ስም በ፯ ግደፍ።

 

      ፩፤ ሲወጣ ሀብታም መሬት ነው ተቀመጥ። ፪፤ ዕድሜህ ያጥርብሃል። ፫፤ ለአንተ ክፉ ነው ጋኔን ይፃረርሃል። ፬፤ ሀብትህ ብዙ ይሆናል ሲሳይም ታገኝበታለህ። ፭፤ ፊት አግኝተህ ኋላ ትደኸያለህ። ፮፤ ደዌና ምቀኛ ይበዛብሃል። ፯፤ በጣም መልካም ነው ሀብትና ሹመት ከጤና ጋር ታገኝበታለህ ተቀመጥ።

 

           

                          12

 

         ሓሳበ ቦታ። ስምና የቦታውን ስም በ፱ ግደፍ

 

      ፩፤ ሲወጣ ኃይለኛ ነፋስ ይነፍስበታል ሐቅለ በዳ ሥፍራ ነው እሳት ቃጠሎና ደንጋይ አለበት ግሩማን ሰዎች ይታዩበታል የእህል በረከትና ሹመት ይገኝበታል የሰላም ዕድሜ ፴፩ ዘመን ያስቀምጣል። ፪፤በቤቱ ትይዩ እሳት የሚያነድ ጋኔን አለ ቀይ መሬት ነው በቀኝ በኩል ምንጭ ይገኝበታል ትንሽ ገደልና ተረተር አለበት በተረተሩና በገደሉ ላይም ሰው ሁሉ ይቆምበታል በዚህ ሥፍራ ላይ የነፋስ በሽታና ዓረር ያስፈራልና አትቁምበት የሆድ መንፋትና የመቅሠፍት በሽታ ያስፈራል የጤና ዕድሜው ግን እስከ ፳፯ ዓመት ብቻ ነው።

 

      ፫፤ ዙርያው የተከበበ ሥፍራ ነው ትልቅ ዱርና አውሬ ውሃና ትንሽ ሜዳ ዛፍም አለበት ከ፮ ዓመት በኋላ ግን ለቆ መሄድ ይሻላል።

 

      ፬፤ በአቅራቢያው ዘንዶና እባብ ይገኝበታል የሚጠጣው ውሃ ዙሪያው የታጠረ ነው በምንጩ ውስጥ ትልቅ ክፉ ደንጊያ አለበት ደንጊያውንም የሚጠብቅ እባብ አለ ውሃውም እንደ ጠበል ነው ከጎረቤትህ ግን ክፉ ሰው አለበት ንግድና ሹመት ይገኝበታል ከ፫ ዓመት በኋላ ያስዘርፋል ዕድሜን በስራይ ያሳልፋል ብርቱ ጥንቃቄ ያስፈልጋል።

 

      ፭፤ በቦታው ላይ ጥቁር ነገር አለበት ከአጠገቡም ጭጫ ዛፍ አለ የምትወጣና የምትገባ አባይ ሴት አለችበት በሩቅ ሲመለከቱት ሰው የሚመስል ዛፍና ደንጊያ አለበት የ፴ ዓመት ዕድሜ ይገኝበታል ስፍራው በመብረቅና ውሃ ያስፈራል።

 

      ፮፤ በምሥራቅ በኩል ትልቅ አውራ መንገድ አለበት ከቤቱ በታች የጎረቤት ምቀኛና ደካማ የሆነ ሰው አለበት ሲወጡና ሲወርዱ ጕራንጉር የሆነ መንገድ አለበት ነገር ግን እኩይ ነው ከ፲፯ ዓመት በኋላ ያስፈራል።

 

      ፯፤ ቦታው ጠባብ ስለሆነ እኽል ለመዝራትና የሰብል አዝመራ ለመሰብሰብ አይመችም ተረተራም ስፍራ ስለሆነ ጭንጫና ጉብታ ጉድባና ክፉ ወንዝ አለበት እኩይ ነው የ፶ ዓመት እድሜ ያውም በጥንቃቄ አለው።

 

      ፰፤ ከቤቱ በላይ መንገድ አለው በደጁና በምድራፉ በወፍጮው አጠገብ ዘንዶ ይገኝበታል ከፍ ያለ ተራራማ ስፍራ አለበት መልካም ቦታ ነው በሰውየው ኑሮና ምክር ሰው ሁሉ ይቀናበታል ቢታገሥ ግን ሃብትና ሹመት ከጤንነት ጋር ደስታና መልካምም ነገር ሁሉ ይገኝበታል ዕድሜውም ፹ ዓመት ይኖርበታል።

 

      ፱፤ በቦታው ላይ ከፍ ያለ ተረተርና ሸንተረር የጥዋት ፀሓይ የሚአርፍበት አለ ከበታቹም ምንጭ አለበት በምንጩም ዳር የሚያፈራ ዛፍና ለአትክልት የሚስማማ መልካም መሬት አለበት የጋኔን ቅሥፈት ያስፈራል ቢጸልይና ቢፈራ ግን ፸፯ ዓመት ይቀመጥበታል።

 

 

                          13

 

                       ሓሳበ ዕጣ

                 

      ስምና የመኰንን ስም የሰማይንም ስም በ፯ ግደፍ።

 

 

      ፩፤ ሲወጣ ተፈጥሮተ መልአክ ትከውን መልአከ ወመኰንነ ወትከውን ከመ መልአክ። ፪፤ ተፈጥሮተ ጠፈር ከመ ጠፈር ትትሌዓል ወትነውህ በክብርከ ከመ ጠፈር። ፫፤ ተፈጥሮተ አዝዕርት ከመ አዝዕርት ወአትክልት ትለመልም ትጸጊ ወትፈሪ ። ፬፤ ተፈጥሮተ ፀሓይ ልዕልናከ ወክብርከ ይበዝኅ ወየዓቢ ከመ ፀሓይ። ፭፤ ተፈጥሮተ እንስሳ እኩይ ውእቱ ወይሬስዩከ ከመ እንስሳ ወዓድግ። ፮፤ ተፈጥሮተ አዳም እኩይ ውእቱ ወይከውነከ መኰንን ዕደወ ከመ አርዌ ምድር። ፯፤ ተፈጥሮተ ዕረፍት እግዚእ አዕረፈ እምኵሉ ግብሩ በዕረፍት ሢመት ሃብት ወሰላም ትረክብ ወትበልዕ በፍሥሓ ወበዕረፍት ወይከውን ለከ ሠናይ።

 

     

                          14

 

                     ሓሳበ ክፍል።

 

      ስምህና ስሙን በ፱ ግደፍ። ፩፤ ሲወጣ ክፍልከ ውእቱ ያፈቅረከ ወይሁበከ ንዋየ ብዙኃ ውድኅረ በነገረ ሰብእ ትትፋለጡ። ፪፤ ሠናይ ንበር ምስሌሁ ያከብረከ ወያሞግሰከ ያፈቅረከ ወየአምነከ ጥቀ። ፫ ኢኮነ ክፍልከ እኩይ ውእቱ ቅድመ ያፈቅረከ ወድኅረ ይጸልአከ። ፬፤ ውእቱ በጽኑዕ ያፈቅረከ ወይሁበከ ንዋየ ብዙኃ ውብእሲቱሂ ትከልአከ።፭፤ ሶበ ይሬእየከ ያፈቅረከ ወሶበ ትርሕቅ እምኔሁ ይረስዐከ ወይጸልአከ መብልዐ ወመስቴ ይሁበከ የሓምየከ ወኢየአምነከ ወንዋየኒ ኢይሁበከ። ፮፤ እኩይ ውእቱ ኢትንበር ምስሌሁ ኢኮነ ክፍልከ ወሪደ መቃብር ያበጽሐከ። ፯፤ ሠናይ ውእቱ በኵሉ አሐደ ጊዜ ለእመ አፍቀረከ ኢይጸልአከ። ፰፤ ኢኮነ ክፍልከ ቅድመ ያፈቅረከ ወድኅረ ይጸልኣከ ባሕቱ በስሙ ንዋየ ታጠሪ። ፱፤ ሠናይ ክፍልከ በበጊዜሁ በሃበ ሃሎ አታብዝኅ ነቢረ ምስሌሁ ባሕቱ ክፍልከ ውእቱ።

 

     

                          15

 

                     ሓሳበ ፍቅር።

 

      ስመከ ወስመ መኰንን በ፱ ግደፍ። ፩፤ ሲወጣ ሠናይ ውእቱ ፍቅር ወሢመት ትረክብ ወያፈቅረከ ጥቀ። ጥቁር ሰው ምቀኛ አለብህ ከጌታህ ጋር በሰው ነገር ትጣላለህ ነገር ግን አትፍራ ተቀመጥ መልካም ነው። ፪፤ ሠናይ ወፍቅር ልዕልና ወሢመተ ትረክብ ሃብት ወበቍዔት ብከ ንበር ምስሌሁ። ፫፤ ሠናይ ውእቱ ያፈቅረከ ወያሞግሰከ ወይሁበከ ንዋየ ብዙኃ ወብእሲቱሂ ትፀልአከ ንበር በጥበብ። ፬፤ ለእመ ይሬእየከ ያፈቅረከ ወሶበ ትርሕቅ እምኔሁ የሓምያከ ሢመተኒ ይሁበከ ወይከውነከ ጸላኤ ወይወርሰከ ድኅረ። ፭ተ ዓመተ ሕድጎ ወተገሓሥ እምኔሁ። ፮፤ ያፈቅረከ ወንዋየኒ ኢይሁበከ ኢትንበር ምስሌሁ። ፯፤ ሠናይ ውእቱ ፍቅር ወሢመት ትረከብ የዓብየከ ወንዋየኒ ይሁበከ ወትዌስክ ጸጋ በዲበ ጸጋ። ፰፤ መብልፅ ወስቴ ይሁበከ ለእመ አልቦቱ ንዋይ ኢትንበር ምስሌሁ። ፱፤ ሠናይ ውእቱ ያፈቅረከ ይሰይመከ ወየአምነከ ወየዓብየከ እምኵሎሙ አግብርቲሁ ኢትትፈለጥ እምኔሁ።

 

                          16

 

                  ሓሳብ ኑሮ ወዕድል።

 

      ስምና የእናትን ስም በ፱ ግደፍ። ፩፤ ሲወጣ በሹመት ይኖራል። ፪፤ በንግድ ይኖራል።፫፤ በዙረት ይኖራል። ፬፤ በእጀ ሥራ ይኖራል።፭፤ በወታደርነት ይኖራል። ፯፤ በብክንክን ይኖራል። ፯፤ በቤተ መንግሥት ይኖራል።፰፤ በዙረትና ልፋት ይኖራል። ፱፤ በንግድና በእርሻ ይኖራል።

 

                          17

 

                     ሓሳብ ውሉድ።

 

      ስሙንና የእናቱን ስሟንና የእናቷን ስም በ፭ ግደፍ።

      ፩፤ ትወልዳለች። ፪፤ አትወልድም። ፫፤ ወንድና ሴት ትወልዳለች። ፬፤ ማሕፀንዋ ዝጉ ማካን። ፭፤ ሠናይ ላህያ ዓቢይ ብሩክ ወዘይሤኒ ባዕል ትወልድ።

 

                          18

 

                    ሓሳበ በረከት።

 

      የሁለቱን ስም በ፬ ግደፍ። ፩፤የሴቲቱ በረከት። ፤፪ የወንዱ በረከት ፫፤ በረከት የላቸውም።፬፤ ጥቂት አላቸው።

 

                          19

 

                   ሓሳበ አንድነት።

 

      ስምህንና ስምዋን በ፰ ግደፍ  ፩፤ መልካም ነው። ፪፤ ወላዋይ ነው። ፫፤ ክፉ ነው። ፬፤ መልካም ፍቅር ነው። ፭፤ መልካም ዕድሜ ነው። ፮፤ ወላዋይ ነው። ፯፤ የመልካም መልካም ነው። ፰፤ ወላዋይ ነው።

 

                          20

 

                   ፪ኛ ሓሳበ ሡሉድ።

 

      ስምዋንና ስምህን በ፰ ግደፍ። ፩ ወንድ ትወልዳለች። ፪፤ ያስወርዳታል። ፫፡፬፤ ሴት ትወልዳለች። ፭ ወንድ ትወልዳለች። ፮፤ ሴት ትወልዳለች። ፯፤ ወንድ ትወልዳለች። ፰ ፤ዘርእ የለም።

 

                          21

 

                     ሓሳብ ፅንስ።

 

      ስምዋንና ስምህን የተረገዘበትንም ወር በ፰ ግደፍ። ፩፤ ዓይነ ጨምጫማ ይወለዳል። ፪፤ ቀይ ሴት ትወለዳለች። ፫፤ ጥቁር ሴት ትወለዳለች። ፬፤ ቀይ ሴት ትወለዳለች ። ፭፤ እግረ ቀጭን ወንድ ይወለዳል። ፮፤ የቀይ ዳማ ወንድ ይወለዳለ። ፯፤ ጥቁር ወንድ ይወለዳል። ፰፤ ራሰ ሸላታ ይወለዳል።

                          22

 

                    ፪ኛ ሓሳበ ኑሮ።

 

      ስምና የእናት ስም በ፯ ግደፍ።፩፤ በሹመት ይኖራል። ፪፤ በመልእክትና በሎሌነት ያድራል። ፫፤ በክህነት ይኖራል። ፬፤ በጽሕፈትና በሴቶች ርስት ይኖራል። ፭፤ በንግድ ይኖራል ፮፤ በሴት ገንዘብ ይኖራል። ፯፤ በቤተ ክህነት ይኖራል።

           

                          23

 

                  ሓሳበ ጉብር (ሎሌ)።

 

      ስምህንና ስሙን በ፭ ግደፍ።፩፤ በመልእክቱ ያስደስትሃል። ፪፤ ተንኰለኛ መካር ነው ያጠፋሃል። ፫፤ ክፉ ነው ይሰርቅሃል። ፬፤ ያሳዝነሃል አይጠቅምህም።፭፤ በሽተኛ ይሆናል።

 

                          24

 

                      ሐሰበ ሙግት

 

      የአንተንና የአባትህን ስም ዕለትና ወርኅ ወንጌዊውንም በ፭ ግደፍ። ፩፤ ይረታሃል። ፪፤ ትረታዋለህ ፫፤ ትታረቃላችሁ። ፬፤ ይረታሃል። ፭፤ ትረታዋለህ።

 

                          25

 

                    ፪ኛ ሐሳበ ጋብቻ

 

      የሁለቱን ስምና የእናቶቻቸውንም ስም በ፰ ግደፍ።

 

      ፩፤ መጀመሪያ መልካም ሁኖ ከአሥር ዓመት በኋላ በጭቅጭቅ ይለያያሉ (ይሞታሉ)። ፪፤ አብረው በሰላማዊ ኑሮ ያልፋሉ። ፫፤ መልካም ነው። ፬፤ ወላዋይ ነው። ፭፤ ክፉ ነው። ፮፤ መልካም ነው። ፯፤ ክፉ ነው። ፰፤ የክፉ ክፉ ነው።

 

                          26

 

                    ፪ኛ ሐሳብ ቦታ።

 

      ስምና የእናት የቦታውንም ስም በ፲፪ ግደፍ።

      ፩፤ መልካም ነው ኑርበት። ፪፤ ወላውል ነው። ፫፤ ክፉ ነው አትቅረብ። ፬፤ የኀዘን ቦታ ነው። ፭፤ እጅግ መልካም ነው። ፮፤ ክፉ ነው። ፯፤ መልካም ነው። ፰፤ ሃብት ሞልቷል ዕድሜ የለም።፱፤ መልካም። ፲፤ ሞት ብቻ። ፲፩፤ ወላዋይ። ፲፪፤ ክፉ ነው አትቅረብ።

 

                          27

 

                    ሐሳበ ባሕርይ።

 

የሰው ባሕርይ በ፭ ይመደባል ስሙን ብቻ በ፭ ግደፍ።

      ፩፤ በአንበሳ ይመሰላል ባሕርዩ ቍጡና ኩሩ። ፪፤ በጎሽ ይመሰላል ባሕርዩ፤ ገራም ሞገሰኛ ምስጉን ጎበዝ። ፫፤ በዝሆን ይመሰላል የረጋ ትዕግሥተኛ ቸርና ቻይ። ፬፤በአውራሪስ ይመሰላል ባሕርዩ ገር የዋህ ጠርጣሪ ተናጋሪ። ፭፤ በነብር ይመሰላል ባሕርዩ ብስጭተኛ ንፉግ ኃይለኛና ነጣቂ።

 

                          28

 

               ሐሳበ ሃብት መኖርያ (ቀበሌ)

 

      ስምና የናትን ስም በ፬ ግደፍ። ፩፤ በምሥራቅ በኩል በአለው በር ተቀመጥ። ፪፤ በምዕራብ በኩል በአለው ቀበሌ ተቀመጥ። ፫፤ በሰሜን በኩል በአለው በር ተቀመጥ። ፬፤ በደቡብ በኩል በአለው በር ተቀመጥ።

 

                          29

 

                    ሐሳበ እስራት።

 

የባለ ጋራህንና የአንተን ስም በ፬ ግደፍ። ፩፤ ትፈታለህ። ፪፤ በጥብቅ ትታሰራለህ። ፫፤ በቶሎ ትፈታለህ። ፬፤ እንደታሰርህ ትሞታለህ።

 

                          30

 

                     ሐሳበ ድውይ።

 

ስምና የእናቱን ስም ወርኁንና ወንጌላዊውን በ፯ ግደፍ።

 

      ፩፤ ይሞታል። ፪፤ በሕማም ይኖራል። ፫፤ ደኅና ይሆናል። ፬፤ ይሞታል። ፭፤ አካሉ ይጐድላል። ፮፤ ብዙ ጊዜ ታሞ ይድናል። ፯፤ በቶሎ ተፈውሶ ይድናል።

 

                          31

 

                   ሐሳበ ዘመቻ (ጦርነት)

 

ስም ቀንና ወርኅን በ፬ ግደፍ። ፩፤ ትያዛለህ ትማረካለህ ትፋጃለህ ትዘረፋለህ ትደሰታለህ ትመሰገናለህ ትሾማለህ ትሸለማለህ። ፪፤ ሠራዊት ያልቅብሃል። በረሃብና ውሃ ጥም ትቸገራለህ ትከበባለህ ይጨንቅሃል ነገር ግን አንተ አትያዝም ታመልጣለህ። ፫፤ ወጥተህ ዘምተህ ተዋግተህ ድል አድርገህ ጠላትህን አስገብረህ አስረህ ማርከህ በአሸናፊነትና ግርማ ታጅበህ ትመለሳለህ። ፬፤ ያይልብሃል ትሸሻለህ አገር ታስደመስሳለህ። ሕይወትህንም ያስፈራሃል።

 

                          32

 

                   ሐሳበ ፍትሕ (ፍርድ)።

 

      ስም የዳኛና የወንጌላዊውን ስም በ፭ ግደፍ።

      ፩፤ በፍጥነት ትረታዋለህ። ፪፡፫፤ ወላዋይ ቀጠሮ ነው።

፬፤ ይፈረድብሃል። ፭፤ ትታረቃላችሁ።

 

                          33

 

                     ሐሳበ ሕሙም።

 

      ስም ወርኅ ወንጌላዊን በ፫ ግደፍ። ፩፤ ይድናል። ፪፤ ሕመም ይበዛዋል አይድንም። ፫፤ በቶሎ ይሞታል።

 

                          34

 

                      ሐሳበ ጋብቻ

 

      ስምዋንና የእርሱን ስም በ፰ ግደፍ። ፩፤ በተባት ይበኰራሉ ብዙ ዘመን ይኖራሉ ይፋቀራሉ አይፋቱም ባልየው በሞት ይቀድማል። ፪፤ በሴት ይበኰራሉ ብዙ ዘመን ይኖራሉ ብዙ ልጆች ይወልዳሉ ሴትዮዋ በሞት ትቀድማለች። ፫፤ ይፋታሉ ይታረቃሉ በመካከለኛው ጊዜ አብረው ይኖራሉ ሀብት ያገኛሉ ሴቲቱ በሞት ትቀድማለች።፬፤ በሴት ይበኰራሉ ብዙ ይወልዳሉ በሰላም ይኖራሉ ሴትዮዋ በሞት ትቀድማለች። ፭ በተባት ይበኰራሉ ትልቅ ሀብት ያገኛሉ እንደውሻ ይናከሳሉ እንደ አህያ ይራገጣሉ ይፋታሉ ይታረቃሉ በጭቅጭቅ አብረው ይኖራሉ ወንድየው በሞት ይቀድማል። ፮፤ በእንስት ይበኰራሉ ብዙ ሴቶች ይወልዳሉ ሀብትን አያገኙም በሰላም ይኖራሉ ሴትዮዋ በሞት ትቀድማለች። ፯፤ በተባት ይበኰራሉ ትልቅ ሀብትና ጤና ያገኛሉ አይጣሉም ይፋቀራሉ በሰላምና በደስታ ይኖራሉ ወንድየው በሞት ይቀድማል። ፰፤ እርስ በርሳቸው አይተማመኑም ይጠራጠራሉ እንደ ውሻ ይናከሳሉ እንደ አህያም ይራገጣሉ ብዙ ሴቶች ይወልዳሉ በመጨረሻው ይፋታሉ ሴትዮዋ በሞት ትቀድማለች።

 

                          35

 

               ፪ኛ ሐሳበ ክርክር ወሙግት።

 

      ስምህን ሌሊትና ዕለትን በ፱ ግደፍ።

 

      ፩፤ ይፈረድብሃል። ፪፤ ይፈረድልሃል። ፫፤ ከቤትህ አትውጣ። ፬ና፭፤ አትሟገት ዳኛ ይጠምሃል። ፮፤ ተጠበቃየ በል። ፯፤ ነገርህን ተገላገል፤ ፰፤ትረታለህ ፱፤ ከብዙ ክርክር በኋላ ትታረቃለህ።

 

                          36

 

              ፪ኛ ሐሳበ ነገራት ወከዊኖቱ።

 

      የባላጋራህና የአንተን ስም የዳኛና የዕለት ስም በ፲፪ ግደፍ።

 

      ፩፤ መልካም ነው ጠብ የለውም። ፪፤ ክፉ ሰዓት ነው። ፫፤ መልካም ቀን ነው ወደ ነገሥታትና መኳንንት ሒድ ይቀናሃል። ፬፤ የደስታ ቀን ነው ብዙ ሰዎች ወደ ቤትህ ይመጣሉ። ፭፤ ክፉ ቀን ነው ጥቁር ሰው ነገርህን ይሰርቅብሃል ተጠንቀቅ። ፮፤ የደስታና የፍሥሐ ቀን ነው። ፯፤ መልካም ቀን ነው። ብትዘራ ያፈራል ከሚስትህ ጋር ተገናኝ ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች ፰፤ ክፉ የሞት ቀን ነው ከቤትህ አትውጣ ተጠንቀቅ። ፱፤ መልካም ቀን ነው ገንዘብ ታገኝበታለህ የትም ሒድ። ፲፤ ክፉ የእስራት ቀን ነው። ፲፩፤ በቀኝ ጐንህ እንደውጋት ያቃጥልሃል። ፲፪፤ የጥቂት ቀን እስራት ነው።

 

                          37

 

       ሐሳበ እህል ውሃ። ስምዋንና ስሙን በ፱ ግደፍ።

 

      ፩፤ ትልቅ ጸጋ ያገኛሉ ብዙ ዘመን ይኖራሉ በተባት ይበኰራሉ። ፪፤ ጊዜ ይፋታሉ በብዙ ጭቅጭቅ በዘመነ ማቴዎስ እሑድ ቀን እህል ውሃቸው ያልቃል።

 

 

      ፪፤ መላሰኛ ናትና አግባት ብዙ ገንዘብ ያገኛሉ በሴት ይበኰራሉ ነገር ግን በቅንአት በዘመነ ማርቆስ እህል ውሃቸው ሰኞ ቀን ያልቃል።

 

      ፫፤ በ፫ ወር በ፫ ዓመት እንደ ውሻ ይናከሳሉ እንደ አህያ ይራገጣሉ ፫ ጊዜ ይፋታሉ ፩ ጊዜ ይታረቃሉ ሴትዮዋ ቀናተኛ ሌባ ዘማዊት ናት ልጅ የላቸውም በዘመነ ሉቃስ ማክሰኞ ቀን እህል ውሃቸው ያልቃል።

 

      ፬፤ ጤናነት ብዙ የለም ሴሰኛና ደረቅ ናት ወደ ኋላ ደግ ትሆናለች ፩ ጊዜ ይፋታሉ በዘመነ ዮሐንስ ሮብ ቀን እህል ውሃቸው ያልቃል።

 

      ፭፤ ገንዘብ የለም በንዝንዝና በቅንአት ይኖራሉ እንደ ውሻ ይናከሳሉ እንደ አህያ ይራገጣሉ ብዙ ልጆች ግን ይወልዳሉ በዘመነ ማቴዎስ በሐምሌ ወር እህል ውሃቸው ያልቃል።

 

      ፮፤ በሃኬት ይኖራሉ መናጢ እንዳትሆን ራስህን ለካህን አታሳይ በዘመነ ማቴዎስ ዓርብ ቀን እህል ውሃቸው ያልቃል።

 

      ፯፤ ራስህን ለካህን አሳይ ንስሐ ግባ ጸልይ በደስታ ይኖራሉ ብዙ ልጆች ይወልዳሉ በሞት ይለያያሉ በዘመነ ሉቃስ ቅዳሜ ቀን እህል ውሃቸው በኃዘን ያልቃል።

 

      ፰፤ በእንስት ይበኰራሉ ንብረታቸው በካና ነው አይመሰጋገኑም ሁልጊዜ ይፋታሉ በቶሎ ይታረቃሉ አይለያዩም ሴትዮዋ በሞት ትቀድማለች በዘመነ ዮሀንስ ቅዳሜ ቀን እህል ውሃቸው ያልቃል።

 

      ፱፤ ፍቅር ያለው መልካም ኑሮ እንደ መኳንንት ሴትዮዋ እንደ ርግብ የዋህና ቸር ናት በተባት ይበኰራሉ ይወልዳሉ በሀብት ይኖራሉ ሴቲቱ እግሮችዋ ቀጫጭን ዓይኖችዋ ጠንጋራ ፩ዱ ወደ ሰሜን ፩ዱ ወደ ደቡብ ያያል ወደ ቀን ካህን ሒዳ ትጠይቅ በቀይ በግ ብራና ሱስንዮስን ለሾተላይ አስጽፋ ብትይዝ ልጆችዋ ያድጋሉ። በዘመነ ማቴዎስ እሑድ ቀን እህል ውሃቸው ያልቃል።

 

 

                          38

 

                     ሐሳበ ሀብት።

 

      የእርሱንና የናቱን ስም በ፬ ግደፍ።

 

      ፩፤ባለ ጸጋ ይሆናል። ፪፤ መጀመሪያ አጥቶ በኋላ ያገኛል። ፫፤ እስከ ዕለት ሞቱ ድሃ ይሆናል። ፬፤ባለጸጋ እጅግ ሀብታም ነው እጁ አይፈታም ለሰው በጣም ንፉግ ነው።

 

                          39

 

                   ፪ኛ፤ ሐሳበ አድባር።

 

      ስምንና የቦታውን ስም በ፫ ግደፍ። ፩፤ እንደ ፀሐይ የበራ ነው። ፪፤ ሰው ይጠላሃል እንደ ውሻ ይነክስሃል። ፫፤ ገንዘብ የለም ልፋት ብቻ ነው።

 

                          40

 

                  ሐሳበ ፍኖት (መንገድ)።

 

      ስምና ወርኅ ቀንንም በ፱ ግደፍ። ፩፤ መልካም ነው ሒድ ምልክቱም ቀይ ሰው ታገኛለህ መብልና መጠጥ ያጋጥምሃል ቀንቶህ ትመለሳለህ። ፪፤ ሒድ መልካም ነው ጥቁር ሰው ያላቸው ሴቶችና ወንዶች ከሽማግሌዎች ጋር ታገኛለህ ትንሽ ጠብና ክርክር ትሰማለህ አንተ ግን ቀንቶህ በደህና ትመለሳለህ። ፫፤ በፍጹም ክፉ ነው እግርህን አታንሣ ዓርፈህ ከቤትህ ተቀመጥ። ፬፤ ሒድ መልካም ነው  ምልክቱ ከብቶች የሚነዱ ሰዎች ታገኛለህ። ፭፤ ክፉ ነው ከነምልክቱ በጐረቤትህ ልቅሶ ትሰማለህ ስለዚህ ዓርፈህ ከቤትህ ዋል። ፮፤ አትሒድ በፍጹም አይቀናህም። ፯፤ ሒድ መልካም ነው ምልክቱም ጥቁር አሞራ በስተቀኝህ ታያለህ። ፰፤ ክፉ ነው አያስደስትምና ከቤትህ ብትውል ይሻላል። ፱፤ መልካም ነው ሒድ ቀንቶህ ትመለሳለህ ከነምልክቱ በጉዞህ ላይ ፈረስና በቅሎ የጫኑ ሰዎች ታገኛለህ ከቤትህ ግን በ፬ ሰዓት ውጣ።

 

                          41

 

                  ፪ኛ ሐሳበ ማደሪያ።

 

      ያባቱን ስም ከኮከቡ ጋር በ፬ ግደፍ። ፩፤ በቤተ መንግሥት ሁኖ በሹመት ያድራል። ፪፤ በሙግትና በጥብቅና በርስት ክርክር ይኖራል። ፫፤ በቤተ ክህነትና በጽሕፈት ሥራ ይኖራል። ፬፤ በንግድና በእርሻ ይኖራል።

 

                          42

 

                     ሐሳበ መካን።

 

      ስምና የእናትን ስም በ፯ ግደፍ። ፩፤ ይዘገያል እንጂ ፩ ብቻ ይወለዳል። ፪፤ በፍጥነት ይወለዳል። ፫፤ እስከ ሞት ድረስ አይወለድም። ፬፤ ብዙ ይወለዳሉ። ፭፤ ይገረዛል ነገር ግን ጋኔን ይበጠብጠዋል። ፮፤ ከቶ አይወለድም። ፯፤ ወንድና ሴት ይወለዳሉ።

 

                          43

 

                  በእንተ ዓይነ ጥላ።

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ። ፩፤ አምላክ።ጸሎተ በእንተ ዓይነ ትላ ወዓይነ ወርቅ ለመግረፊ ፀር ወሾተላይ እግዚኦ ሚበዝኁ እለ ይሣቅዩኒ ብዙኃን ቆሙ ላዕሌየ የሚለውን በሞላው ጽፈሕ በባሕር ዓረብ ሰፍተህ ክታቡን ያዝ።

 

                          44

 

                  ፪ኛ ሐሳበ ትንቢት።

 

ስምና የእናትን ስም ወንጌላዊውንና ዓ.ም በ፱ ግደፍ።

 

      ፩፤፪ በቤትህ ቆይ ሰው ይታመምብሃል ሰው ከሚቀርበት ጕድጓድ ብቅ ብለህ አትይ ሞት ያስፈራሃል በጥቅምትና በኅዳር ተጠንቀቅ በየመባቻው ደም አፍሥ ደኅና ይሆንልሃል። ፫፤ በመስከረምና በየካቲት በግንቦት የከብት ጥፋት አለብህ በሌላም ወር የዘመድ ኃዘን ያገኝሃል። ፬፤ በታኅሣሥና በየካቲት ትታመማለህ በሽታህ ሰው ያደክማል እንጂ ትድናለህ ከብትም ይጠፋብሃል ነጭ ነገር እረድ። ፭፤ የእግር በሽታ ወይም ቁስል ያገኝሃል የጥር ሥላሴ ቀን ተጠንቀቅ ጀምበር ስትጠልቅ የተገኘ ገንዘብ ይጠፋብሃል በጥቅምትና በጥር በግንቦት ተጠንቀቅ ብረት ሳትይዝ ወደ ደጅ አትውጣ። ፮፤ እንደ ሦስት ነው ይስማማዋል። በ፯ በመጋቢት ትታመማለህ በነሐሴ እንደሆነ ግን ያስፈራሃል በጥብቅ መጠንቀቅ ይገባሃል። ፰፤ ያባትና ያያት ሞት የ፯  ትውልድ ኃዘን ያስፈራሃል በሐምሌና በነሐሴ ተጠንቀቅ። ፱ ሆድህን ያምሃል በሽተኛ አትይ ወዲያው እግዚኦ የሚያሰኝ ጉድ እንዳያገኝህ ኅዳርንና ሚያዝያን ሰኔን ፳፰ ቀን አጥብቀህ ተጠንቀቅ። ጠላትህን ግን ታሸንፈዋለህ ትረታዋለህ።

 

                          45

 

                   ሐሳበ ቤተ ንጉሥ።

 

      ስምና የእናትን ስም ወርኅና ዕለትን በ፫ ግደፍ። ፩፤ መልካም ነው ይቀናሃል በደስታ ትገባለህ። ፪፤ ገንዘብ ይጠፋብሃል ኃዘን ያገኝሃል። ፫፤ ችግር ረኃብ በሽታ ይቆይሃል።

 

                          46

 

                  ሐሳበ ምሥያጥ (ንግድ።)

 

      ስምና የእናትን ስም በ፱ ግደፍ። ፩፤ በዕንቅብ። ትነግዳለህ ፪፡፫፤ በፍየል። ፬፤ በበግ። ፭፤ በፈረስ በበቅሎና በአህያ። ፮፡፯ በዶሮ። ፰፤ በላምና በበሬ። ፱፤ በእህል በወርቅ በምድር።

 

                          47

 

                  ሐሳበ ሰራቂ (ሌባ።)

 

      ስምህንና የሌባውንም ስም በ፱ ግደፍ። ፩፤ ከቤት ሰው ወስዶት ይገኛል። ፪፡፫፤ ከቤትህ ፈልግ ታገኘዋለህ። ፬፤ ሌባውን በምልክት ታገኘዋለህ። ፭፤ ከምትጠረጥረው ቤት አትሒድ ፀሐይ ሳትወጣ በደጅህ ይጥልልሃል። ፮፤ ብትፈልግ ታገኘዋለህ። ፯፤ አይገኝም አትድከም። ፰፤ ሀገር ለሀገር ሲዞር ታገኘዋለህ። ፱፤ የጐረቤት ሰው ይዞት በድንገት  ታገኘዋለህ።

 

                          48

 

                   ሐሳበ ሕሙም ወዕለት።

 

      ስምና የእናትን ስም ወርኁንና ወንጌላዊውን በ፯ ግደፍ።

 

      ፩፤ ሲወጣ እሑድ ቀን ነው የተገኘው ከፈሳሽ ውሃ ፀሐይ ሞቅ ሲል ለከፈው። እስከ ፲፪ ቀን ድረስ ያስፈራዋል ከዚያ ካለፈ ይድናል በሽታው ሲጀምረው በሞላ አካላቱ ይበተናል እጁን እግሩን ወገቡን ይቈረጥመዋል በኋላ ግን ያስታውከዋል ነስር ውጋት ራስ ምታት ቁርጠት ያመዋል እግሩን ይሸመቅቀዋል ብርድ ብርድ ይለዋል በሽታው በሆኑ ይጸናበታል መድኃኒቱ ግን እንደ ኮከብ በግምባሩ ነጭ ያለበት ጥቁር በግ ከደሙ ይጠጣ ወይም ነጭ ዶሮ አርዶ ይጣል።

 

      ፪፤ ሰኞ ዕለት ሌሊት ሲወጣ ወይም ውሃ ሲታጠብ ወይም ከበር አፍ  ለሽንት ማልዶ ሲወጣ ለከፈው በሽታው ረዥም ነው ራሱን ወገቡን እጁን እግሩን በሞላ አካላቱ ተሰራጭቶ እያድቀሰቀሰ እያለ ዘበ ያመዋል። በሽታው ውጋት ቁርጠት ነስር ደም ትውኪያ ተቅማጥ ይጸናበታል እስከ ፲፪ ወይም ፳ ቀን ድረስ ያስፈራዋል። የወጋው የውድማ ዛርነው ከቈየ ቁስል ይለዋል በልጅነቱ መልከፍትና ዓይነ ጥላ አለበት የስለት ገንዘብ አለውና ይክፈል መድኃኒቱ በኮከቡ ያለው ጽሕፈት ነው ቀይ ዶሮ አዙረህ አርደህ ጣልለት።

 

      ፫፤ ማክሰኞ ቀን በደም ተወጋ ወይም ነጭ ነገር ይዞ ከአመድ ላይ ሁኖ ለከፈው። የወጋውም፤ ከዛር የተወለደ ድርካቡ የሚባል ጋኔን ነው። በሽታው ሲጀምረው እራሱን ወገቡን ልቡን ሆዱን ነው ተቅማጥ ትውኪት ንስር አለው ቈይቶ በሰውነቱ እበጥ ያመዋል ይጸናበታል እስከ ፲ ቀን ድረስ ያስፈራዋል። ወደ እግዚአብሔር ይጸልይ ለ፫ ቤተ ክርስቲያን ዕጣን ዘቢብ ይሳል ቀይ ያልተጠቃች ፍየል ይብላ ቀይ ዶሮም አርደህ ጣልለት።

 

      ፬፤ ሮብ ቀን ከማዕድ ላይ ሲበላ ወይም ውሃ ሲታጠብ ተለከፈ ሴት ጋኔን ወጋችው ቡዳም አለበት ራሱን ወገቡን ሆዱን ልቡን ያመዋል ሰውነቱን ሁሉ ብርድ ብርድ ይለዋል በሙሉ ገላው እየወጋ ይቈረጥመዋል ተቅማጥ ነስር ትውኪያ አለው  ቆይቶ ሰውነቱ ሁሉ እያበጠ ያዝ ለቀቅ ያደርገዋል በመጀመሪያ እንደ ታመመ እስከ ፲፪ ቀን ድረስ ይጸናበታል ራሱን ያዞረዋል እንደ ቅጀት ያደርገዋል ብርቱ ውጋት ይሰማዋል ፩ ዓመት ከመንፈቅ ሲሆነው ይሞታል። መድኃኒቱ የሰይጣን ዶሮ ሥጋውንና ጠጕሯን ይታጠን ለዕለት ይሻለዋል ቀይ ዶሮ ቀይ በግ  ዳልቻ ፍየል ዳለቻ በግ ልበ ወርቅ ዶሮ ገብስማ ዶሮ ቡሃ በግ ያፍሥ በኮከቡ ያለውን ሁሉ መድኃኒት ቢያደርግ ይሰምርለታል።

 

      ፭፤ ሓሙስ ቀን አባ መጋል የሚባል የመቃብር ጋኔን ራሱን በጭራ መቶት ለክፍቶታል በሕልሙም አስደንግጦታል ሓሙስ ወደ ማታ ነው የጀመረው ራሱን ጫንቃውን ልቡን ግራ ቀኝ ጐኑን ይወጋዋል እስከ ፲፪ ቀን ድረስ በጸና ይታመማል ይህን ከአለፈ ግን ሞት የለበትም። ራሱን እያዞረ ያቃጀዋል መድኃኒቱ በኮከቡ እንደ ተጻፈው ነጭ ዶሮ የቀይ ዳለቻ በግ  ይረድ ጥቁር ነጠላ ዶሮ አዙሮ አርዶ ይጣል።

 

      ፮፤ ዓርብ ቀን ወደ ደጅ ሲወጣ ተለከፈ ከፈሳሽ ውሃ ወጥቶ ከአመድ ላይ ሁኖ አገኘው  በነጭ ነገር ነው የለከፈው የቡዳ ዘር አለበት ልቡን ይነሣዋል ቅጀት ይጸናበታል ራስ ምታትና ውጋት የሆድ ቁርጠት አለው በሞላ አከላቱ ይቈረጥመዋል ያደቀዋል ጥርሱን ያጋጨዋል ጥፍሩን ይመጠምጠዋል ነስር ተቅማጥ እባጭ ትውኪያ ይበረታበታል ከልጅነቱ ጀምሮ አብሮ አደግ በሽታ ነው አትድከም ይሞታል።

 

      ፯፤ ቅዳሜ ቀን ያመድ ቀላይ ጋኔን ለከፈው  ጥላውን እንደ ደመና ጣለበት ደሙን ይመጠምጠዋል ራሱን ልቡን ግራ ቀኝ ጐኑን ያመዋል በሞላ ካላቱን ይቈረጥመዋል ቅጀት ውጋት ይጠጋበታል ትውኪያ ነስር ደም ይፈታበታል ሴት ዛር አለችበት  ከልጅነቱ ጀምሮ ዓይነ ጥላ አለበት  መድኃኒቱ በኮከቡ እንዳለው ነው። ነጭ ዶሮ በግ ዳለቻ ፍየል እረድለት ከየብልቱ ሰው ሳይቀምሰው ጠብሰህ ወደ ዱር ጣልለት። የሰው ጐሜ (ቂም) አለው  ይቅር ይበሉለት ስለትም አለበትና ይክፈለው።

 

                          49

 

                    ፬ ሓሳበ ሕሙም።

 

      ስምና የእናትም ስም በ፭ ግደፍ። ፩፤ በሠርክ በ፱ ሰዓት ጀመረው ይሳል ይጸልይ በጽኑ ይታመማል ደም ይከተለዋል እኩይ አሺሽ ነው። ፪፤ ቀን በ፫ ሰዓት አገኘው ቀትር ጀመረው። ፫፤ ጀምበር ሲጠልቅ  አገኘው ይድናል። ፬፤ በነግህ አገኘው ያሸሻል ወላዋይ ነው። ፭፤ በውድቅት አገኘው አይተርፍም በ፭ኛው ቀኑ ይሞታል።

 

              ሐሳበ ፊደል ወፍካሬ ጠባያት።

 

      ሐሳበ ፊደል ማለት፤ የሰውን ስም መጀመሪያ በሚገኘው በ፩ዱ ፊደል ብቻ ባሕርዩና ጠባዩ ሊገኝና ሊታወቅ ይቻላል ማለት ነው።

 

      ሀ ፩፤ ብሂል፤ ሃይማኖት ጽኑዕ ሠናይ ለሰብእ ሐዋሪ ወፈላሲ ይከውን ዝብጠት ወተኃይዶ ይረክብ ነጋዲ ወሐያዲ ውእቱ ንጹሕ ነፍሱ ንዋዮ ኢይሁብ ለባዕድ ዘረከበ ለርእሱ ይሴሰይ የአስርዎ መኳንንት ወእምርሑቅ ይዴግንዎ በህየ ይትሐመም ይድኅን ወይረክብ ክብረ አቡሁ ኵሎ ንዋዮ ወእንሰሳሁ ወኵሉ ቤቱ ይከውን ሎቱ።

 

      ለ ፪፤ ብሂል፤ ለባዊ ውእቱ ኃይል ወጽኑዕ ወይረክብ ሢመተ ፱ተ ዓመተ ይሠየም ዘርሑቅ ወዘቅሩብ ወኵሉ ብሔረ ሰብእ ይሰግዱ ሎቱ ወይመጽኡ ኀቤሁ ጸላእቱ ወይቀንዮሙ እምድኅረ ሢመቱ የዓሥሥ (ይትዔገስ) ብዙኃ ጊዜ ወይነብር ፸ወ፱ተ ዓመተ ወድኅረ ይመውት በመቅሠፍት።

 

      ሐ ፫፤ ብሂል፤ ሐዋዝ ይከውን በንእሱ ሢመት ይረክብ ነገሩ ነቢብ ወማእምር ውእቱ የአስርዎ ወይወስድዎ ብሔረ ባዕድ በህየ ይነብር ፫ተ ዓመተ ወበ፮ቱ ዓመት ይትመየጥ ብሔሩ ወይሰመይ ወይነ ብር ላዕለ ምድረ አቡሁ ብዙኃ ክብረ ይረክብ በእዱ ትእምርት ሀሎ ቦቱ ብዙኃ ንዋየ ያጠሪ በትዕግልት በቤቱ እስከ ዓመት ኃዘን ይረክብ ፮ተ ጊዜ የኃዘን ወይመውእ ጸላእቱ ወእምድኅረዝ ፯ተ ዓመተ በፍሥሐ ይነብር ወድኅረ በተፊአ ደም መዊት ያፈርሆ።

 

      መ ፬፤ ብሂል፤ ማእምር ውእቱ ማእምረ ሠናየ ወይትኤዘዝ ለአዝማዲሁ በቤቱ ወበውሉዱ ቅድመ የኀዝን ወድኅረ ይትፌሣሕ ወይመውዖሙ ለጸላእቱ ምስለ ብእሲቱ ይትበአስ እምድኅረ ፴ ወ፰ ዓመት ያወስብ ቀይሕተ ብእሲተ ወምስሌሃ ብዙኃ ወርቀ ወንዋየ ያጠሪ በደጋማይ እግሩ ትእምርት ሀሎ ቦቱ ወጸጋማይ እዱ ጸኒን ይቈስል እምድኅረ ልህቀ ያፈቅር በሐውርተ ሠናይ መዋዕለ ይሬኢ አቡሁ በላዕሌሁ ይገብር መዓተ ኢይፈርሆ ለአቡሁ ወለአዝማዲሁኒ ደፋር ውእቱ ሢሳየ ኢየኃጥእ።

 

      ሠ ፭፤ ብሂል-፤ ሥርግው ብእሲ ውእቱ ሠናየ መዋዕለ ይረክብ ያፈቅር ትምህርት ቃለ እግዚአብሔር ይሤንዮ መዋዕሊሁ የአምር ጽኑዕ ውእቱ ነገሩ ወይረድኦ አምላኩ በኵሉ ተግባሩ ወይወርስ ምድረ አቡሁ ወአኀዊሁ። ድኅረ በብእሲቱ ወበቤቱ በውሉዱ ወበርእሱ ኃዘን ይረክቦ። ሀገር ባዕድ ይነብር ብሔረ ሊሉየ ፮ተ ዓመተ  ይጸንሕ በኀቤሁ ፍርሃት አምላኩ አልቦ ወይመውቱ ሎቱ ጸላእቱ ሕማመ ልብ ወሰዓል ሀሎ ቦቱ ዝ ሕማም ይጸንዕ በላዕሌሁ በተፊአ ደም መዊት ያፈርሆ።

 

      ረ ፮፤ ብሄል ረጋሚ ርቱዕ ልቡ ወግብሩ ሠናይ መፍቀሬ ሰብእ ወበዝ ይረክብ ስብሐተ ወሞገሰ በኀበ ኵሉ ሰብእ ሠሐቂ ይከውን በምግባሩ ያፈቅርዎ ሰብእ በብእሲቱ ወበውሉዱ የኀዝን ይብዕል  በእክል ድኅረ ያወስብ ኅሪተ ብእሲተ ወይወልድ በቍዐ ድምድማሁ ወፅሕሙ ብዙኅ ይከውን ማእምረ ወጠቢበ ወምእመነ ይከውን በኵሉ መዋዕሊሁ ያፈቅርዎ መኳንንት ኵሎ ንዋዮ ወጥሪቱ ወቤተ አቡሁ ይወርስ ብዙኃ ክብረ ወሞገሰ በቍዐ ይረክብ በፍሥሓ ወበሐሤት ይሤኒ መዋዕሊሁ።

 

      ሰ ፯፤ ብሂል፤ ስቡሕ ይከውን እምንእሱ ወጽኑዕ ልቡ ነገሩ በኀበ እግዚእ ርቱዐ ይከውን ማእምር ወጠቢብ የኃሥሥ ትምህርተ ርእሶ እደዊሁ ወእገሪሁ ሠናያት ብሔረ ባዕድ የሐውር ወእሙ ተኃዝን ቦቱ ወድኅረ ይገብእ ብሔሮ ዘላዕለ አኃዊሁ ይመውዕ ወይወርስ ምድረ አቡሁ ዓቢይ ሕማም ሀሎ ቦቱ እምድኅረ ደዌሁ ፴ ዓመተ ይነብር ወያወስብ ቀይሕተ ብእሲተ ይብዕል በንዋይ ወይትፌሣሕ ብዙኃ።

 

      ቀ ፰፤ ብሂል ቀዊም ሠናይ ይከውን ማእምረ ወጠቢበ ወልቡ ነዊሐ የሀሊ ባሕቱ መፍቀሬ ንዋይ ይከውን በእንተ ንዋይ ይትበአስ ምስለ አቡሁ ወአኃዊሁ የአስርዎ ብዙኃ ጊዜ ወእምድኅረዝ ይትፈታሕ ወይገብእ ሀገሮ ወይወርስ ክብረ አቡሁ ብእሲቱ ትነብር በሥቃይ ወሞቱኒ  በብካይ ወበገዓር ይከውን ወውሉዱኒ ህየንተ አቡሆሙ ይነብሩ በህየ ይትባዝኁ ይወልዱ ወይብዕሉ።

 

      በ ፱፤ ብሂል ባዕል ወልዑል ውእቱ ባዕድ ብሂል ሐዋሪ ወፈላሲ በኵሉ ሀገር ምእመን ወጠቢብ እምብሔረ ባዕድ ያወስብ ብእሲተ ኅሪተ ይወልድ ውሉደ አንስተ ወይነብር በህየ ትእምርት በየማኑ ሀሎ ያፈቅርዎ ኵሉ ሰብእ ወይነብር በጥበብ ወያጠሪ ብዙኃ ንዋየ ወ፪ተ ጊዜ ይጠፍእ ንዋዩ ወእም ድኅረዝ ይትመየጥ ኀበ ብእሲቱ ወይረክብ ብዙኃ ባቍዐ ወጥዒና ብሔረ ሰብእ ያፈቅር ወኵሎ ዘሐለየ ይሠምር ሎቱ በቃሉ ወበነገሩ ኵሉ ሰብእ ያፈቅርዎ ወይነውሕ መዋዕሉሁ በፍሥሐ  ወበሰላም ይምውት።

 

      ተ ፲፤ ብሂል፤ ተግሣፀ ያፈቅር በጥበብ ይነብር ቤተክርስቲያን የዓቅብ በቀዳሚነት ብእሲቱ የኃዝን ቀዲሙ ያጠፍእ ንዋዮ ወድኅረ ያወስብ ፪ተ ብእሲተ ወክልኤሆሙ ይከውኑ እኩያነ ወሐዋርያነ ይተምዕ ቦሙ ወኢይሰምዕዎ ብዙኃ የኀዝን ቦሙ ወድኅረ ይትፌሣሕ ንዋየ አቡሁ ያጠሪ በእደ ጥበብ ሢመተ ይረክብ እምሀገረ ባዕድ ይሴሰይ በእንተ ንዋዩ ይጸልእዎ ኵሎሙ ሰብአ ብሔር ወወእቱኒ በቃሉ ያደክሞሙ።

 

      ኀ ፳፤ ብሂል፤ ኃይል ውእቱ ይፈርኅዎ ኵሉ ሰብእ በጊዜ ኵናት ቃሉ ሠናይ ለሰሚዕ ወሶበ ይሬእይዎ ገጾ ያፈርህ ጥቀ ያፈቅርዎ ኵሉ ሕዝብ ወርቱዕ ይመስል ለአቡሁ ወለእሙ ባቍዐ ይከውን ወእሙሰ ተኃዝን ላዕሌሁ ወእግሩ ዕቅፍት ውእቱ ወእቅፍቱኒ ያበጽሖ እስከ ለሞት በውሉዱ የኃዝን በዕለተ ልደቱ ይገብእ ውስተ ምድረ አቡሁ ወያፈቅርዎ ሕዝብ በኵሉ መዋዕሊሁ ወይብልዎ ሠናየ ፶ ወ፰ አው ፸ ዓመት ይከውን መዋዕሊሁ።

 

      ነ ፴፤ ብሂል፤ ንጉሠ ይከውን ይብልዎ ሠናይ ብእሲ ወንጹሕ ምእመን ወማእምር ለባዊ ወጠቢብ ወይምህር ኵሎ ሰብአ የሐውር ብሔረ ባዕድ ወየኀዝኑ አቡሁ ወእሙ ወኵሎሙ አዝማዲሁ ውእቱኒ ይትፌሣሕ ጥቀ ወያጠሪ ብዙኃ ንዋየ ወበዘይነብር መካን ቦቱ ይሴንዮ በኵሉ መዋዕሊሁ ይረክብ ሠናየ በጾም በጸሎት ወበምጽዋት ይሠረይ ሎቱ ኃጢአቱ ንጽሕተ ወቅድስተ ትከውን ኵሉ ሰብእናሁ።

 

      አ ፵፤ ብሂል፤ እግዚእ ይከውን በቀዳሚ የኀዝን እስከ ይበጽሕ ለሐፂን ወድኅረ የዓብይዎ ወያከብርዎ ኵሎሙ ሰብእ ወይከውን ሥዩመ ላዕለ ኵሉ ሕዝብ ወይሰምይዎ ኵሎሙ ሰብአ ሀገር በሠናይ ወበክብር እሙን ወኄር  በኵሉ ምግባሩ ኢይለክፍ ምንተኒ ሰብእ በእኩይ ነገር ፍርሀተ እግዚአብሔር ሀለው በልቡ ወጸላእቱሰ ዘልፈ የሐምይዎ በነገረ ሐሰት ወእግዚአብሔር ኢየሐድጎ በእንተ ሠናይ ጽድቁ ወእምድኅረዝ አመ ወሰድዎ ኃያላን በመንፈቀ ዕለት በጽምአ ማይ መዊት ያፈርሆ ወለእመ ድኅነ እምዝ ፷ ወ፮ተ ዓመተ ይነብር።

 

      ከ፶፤ ብሂል ክቡር ብእሲ ይከውን ይትበሀል ሐማዪ ወዓማፂ ዘማዊ  ወሐሳዊ ቃሉኒ ወነገሩ ኢይጥዕም ለሰብእ ፮ተ አንስተ ያወስብ ፲ተ ወ፬ተ ይወልድ ወመንፈቆሙ የሀልቁ ወእለ ተርፉ ይበቍዑ ሎቱ ወየሐውር ኀበ ካልእ ሀገር ይረክብ ክብረ ቀሲሳን ወመኳንንት ወድኀረ ይፈቅድ የሐሊ ምንኵስና ወይትመየጥ ልቡ ኀበ እግዚአብሔር በሊሉይ ሀገር ይረክብ ክብረ ወይሬኢ ሠናየ ዕለተ ወይትፌሣሕ ሐራሲ ይከውን ጥቀ ይዘርእ አክለ ወይረክብ ፍሬ ብዙኅ።

 

      ወ ፷፤ ብሂል ወጣኒ ወፈጻሚ ጽኑዕ በቃሉ ኰናኒ ለኵሉ ይከውን እግዚአ ባሕቱ ድኅረ  እኩይ ይከውን ግብሩ በ፴ ዓመት መዊት  ያፈርሆ ወለእመ ድኅነ ያወስብ ብእሲተ ዘአልባቲ ሐፍረት እኪት ወፀሩ ይእቲ ወእምኔሃ ይወልድ ፯ተ። ልቡናሃ መኳንንተ ወመሳፍንተ ይሔሊ ትሜንኖ ሎበእሲሃ ወውእቱኒ ይረክብ ሢመተ ወይቀንዮሙ ለጸላእቱ ወእምድ ኅረዝ ያወስብ ብእሲተ መካነ ቀያሕ ወኅሪት ወይወልድ እምኔሃ ፬ተ ውሉደ ወይከውኑ ነሳትያነ ገጹ ወንዋዩ ርቱዐ ይከውን ወጸላእቱኒ ይወድቁ ታሕተ አገሪሁ ሕማመ ዓይን ያፈርሆ።

 

      ዐ ፸፤ ብሂል፤ ዓቢይ ወክቡር ያፈቅርዎ አቡሁ ወእሙ በኵሉ መዋእሊሁ ውሉደ ሠናየ ወብእሴ ርቱዐ ይትበሀል አመ ሖረ ውስተ ካልእ ብሔር በነገረ ብእሲተ የኃዝን ወየኃልቅ ንዋዮ ወአልቦ ካልእ ዘይበቍዖ አልቦ ዘይተርፍ እምኵናኑ ይጠፍእ ኵሉ የኃዘን በተሚዕ ይትሐመም ዓቢየ ሕማመ ለእመ ተርፈ ወሐይወ ያፈቅር ፀብአ ወቀስተ ወተቃትሎ ወእምድኅረዝ ይከውን ተዓጋሤ ወጠቢበ ዓቢየ ማእምረ ወመኰንነ ወያፈቅር ጸሊመ ወቀይሐ ወያወሥእ ጥዑመ ቃለ ወይከውን ምግባሩ ዘከመ ንእሱ ወያፈቅር ምድረ አቡሁ ወእሙ ወእምድኅረዝ ሐዊረ የሐድግ ወይሠየም ሢመተ ዓቢየ በርስዓኑ ወይሬኢ ሠናየ። ይከውን ዕድሜሁ ፷ ወ፭ተ ዓመተ።

 

      ዘ ፹፤ ብሂል፤ ይዜከር ወኢይረስዕ ይከውን ፍሡሐ መፍቀሬ ፍሥሓ ውእቱ ብዙኃን ሰብእ ይመጽኡ ኀቤሁ በትምህርቱ ወበጥበቡ ያፈቅርዎ ይሬኢ ድቀተ ጸላኢሁ ወአዝማዲሁ ኵሎሙ ያፈቅርዎ ወይ ሴስይዎ በእንተ አእምሮቱ ብዙኃ ንዋየ ይረክብ በኵሉ መዋዕሊሁ ሞገሰ ወጸጋ ይረክብ ኢየኃጥእ ምንተኒ ባሕቱ መፍቀሬ ንዋይ ወበየውሃቱ ቦቱ አርዌ ይብልዎ ጸላእቱ ኵሉ ሰብእ ያፈቅሮ በእንተ ጥበቡ ወጣዕመ ልሳኑ ወኢይሬኢ ኅልቀተ አዝማዲሁ በካልእ መካን ይሰምዕ ሞቶሙ ወይሠውዕ ሎሙ ለአዝማዲሁ ኀበ ዘኢይቴእይዎ።

 

 

      የ ፺፤ ብሂል፤ የዋህ ይከውን ይብልዎ ወይሬኢ ኵሎ ነገረ ኅቡአት በየውሃቱ ዘወልዶሙ ውሉዱ ይትለአኩ ለቤተ ክርስቲያን ወያፈቅርዎ ነገሥት ወመኳንንት ሥሙር ወሠናይ በኵሉ ዘርአ እክል ይከውኖ ሎቱ ወብዙኃ የኀዝን በእንተ ምግባር ለብእሲቱ ወይከውን ምስማዐ ጕርዔሁ የሐምም ወየሐብጥ ወያብጽሖ ለመዊት ወለእመ ድኅነ እምዝ ፴ ወ፯ተ ዓመተ ይነብር ወያወስብ ቀይሕተ ብእሲተ ወይወልድ እምኔሃ ብዙኃን ውሉደ ወእምዝ ይነብር በብዙኅ ፍሥሓ።

 

      ደ ፻፤ ብሂል፤ ድልው በኵሉ ሠናይ ራእዩ ቅድው ወርቱዕ ሰብእናሁ ቀይሕ ኅብሩ እገሪሁ ነዊሕ ወግሩም ነፍሱ ዓቢየ ውሉደ ይወልድ ወይትበአስዎ መኳንንት ወይከውን ለኵሉ ሰብእ ፀወነ ሠናየ ይወርስ ንዋየ አቡሁ ወአዝማዲሁ ወያወስብ ብእሲተ እኪተ ወያፈቅራ ጥቀ ወይመክሩ ላዕሌሁ ጸላእቱ ከመያኅጕልዎ እመ ድኅነ እምእደ ጸላእቱ ብዙኃ ዘመነ በፍሥሓ ወበሰላም ይነብር ወመዋዕለ ዘመኑ ፷ አው ፸ ዓመተ ይከውን።

 

      ገ ፪፻፤ ብሂል፤ ግሩም እስከ ይልኅቅ የዓጽብ ዓቢይ ምንዳቤ ይረክቦ እመ ድኅነ እምንዳቤሁ ርእሰ ይከውን ብዙኃ ጥሪተ ያጠሪ ይወርስ ቤተ አቡሁ ወንዋየ አዝማዲሁ ወያወስብ ፫ተ አንስተ ዘቀዳሚት እኪት ይእቲ ወዘቀዳሚት ትኄይሶ ብዙኃ ውሉደ ትውልድ ሎቱ ያፈቅር መናብረተ ፮ተ ዓመተ ይነብር በክብር ወበሞገስ ወኵሎሙ ጸላእቱ ይገብኡ ሎቱ ታሕተ እገሪሁ በመዋዕሊሁ። ቅድመ በንእሱ ዓቢይ ዓባ ይረክቦ ወድኅረ ይብዕል እምድኅረ ልኅቀ ሠናይ ምኵናን ይረክብ በማእከላይ ዘመኑ እግዚአ ይከውን ባሕቱ እምድኅረዝ ይጼነስ የኃዝን ወይፈልስ እምብሔሩ ወኀበ ሀገሩ ኅዳጥ ሕማም ይረክቦ ወእምድኅረዝ ይትሌዓል ጥቀ ይነውሕ መዋዕሊሁ ወያፈቅሮ ሰብእ ወይሰምዕዎ ቃሎ ወሶበ ይሬእይዎ ገጾ ይፈርኅዎ ኵሉ ሰብእ ጽኑዕ ልቡ ወኄር በሰብእ የኀዝን ወይፈልስ ኀበ ካልእ ሀገር በህየ ይረክብ ጸጋ ወሞገሰ ወይረክቦ ዓቢይ ደዌ ዘያበጽሖ ለመዊት ወእምነዝ እመ ድኅነ ፵ ወ፯ተ ዓመተ ይነብር ወእምዝ የሐምም ለመዊት ወብእሲቱ ተኃዝን ቦቱ መኳንንት ይሞቅሕዎ ውእቱኒ ይትፌሣሕ ወይሬኢ ሠናየ መዋዕለ። በ፷ ወ፭ ዓመቱ በሰላም ይመውት።

 

      ጠ፫፻ ብሂል ጠቢብ ወጠዋይ ውእቱ ዘነገርዎ ኢይሰምዕ ትእምርት ሃሎ በእግሩ ትእዛዘ ኢያፈቅር ወኢይትኤዘዝ እምንእሱ ቃሉ ጥዑም ወሠናይ ዘሰአለ ኢየቃጥእ በኀበ ነገሥት ወመኳንንት ይረክብ ንዋየ በሕቱ ደዌ ቦቲ እመ ድኅነ ድኅረ ብዙኅ ጊዜሎቱ በረከት ወጥዒና ኢይጼነስ ወኢየኃዝን።

 

      ጰ ፬፻፤ ብሂል ፤ ጳዝዮን ዕንቍ ሠናይ ብእሲ ይብልዎ ተዓጋሢ በኵሉ ነገር ወልቡ ይሔሊ ብዙኃ የአምር ኵሎ ግብረ ዓለም ወይትበቋዕ በርእሱ ፵ ዘመነ ይነብር አቡሁ ወእሱ የኃዝኑ ቦቱ ይከውን ቀፍሊ በውሉዱ ፬ ይወልድ ፪ ይመውቱ ወየኃውሩ እምኔሁ ኵሉ ሰብዓ ቤቱ ወይፈልስ ብሔረ ባዕድ ማዕከለ ብዙኃን ይነብር ወይመውቱ ሰብአ ቤቱ በዝንቱ ነገር የኃዝን ባሕቱ ለርእሱ በጥዒና ይነብር እምድኅረዝ ዘይከውኖ እግዚአብሔር የአምር ነገሩ።

 

      ጸ ፭፻፤ ብሂል ጻድቅ ብእሲ ሠናይ ሰብእ እምን እሱ ኵሉ ሰብእ ያፈቅርዎ ላሕይ ወሠናይ ገጹ እግሩ የሓምም በ፴ ዓመቱ ወአቡሁ የኃዝን በእንቲአሁ ወአመ ሓየሶ ደዌሁ ብዙኃ መዋዕለ ይነብር ዓቢይ ጻድቅ ወየዋህ ይከውን በእዴሁ መዊት ያፈርሆ።

 

      ፀ ፮፻ ፤ ብሂል ፤ፅዱል ወብሩህ ወንጹሕ በሥጋሁ በአንተ ሠናይ ምግባሩ ያፈቅርዎ አቡሁ ወእሙ ወኵሎሙ አዝማዲሁ ብዙኃ ንዋየ ይረክብ ባሕቱ መኳንንት ይሞቅሕዎ ወይፈትሕዎ ወእምዝንቱ ነገር ያጠሪ ጥሪተ ብዙኃ ጸላእቱ ይበዝኁ ከመ ሣዕር ወኢይገብርዎ ምንተኒ ይገብኡ ታሕተ እገሪሁ ባሕቱ መፍቀሬ ንዋይ ይከውን ድኅረ ጸንሐ ፸ወ፰ ዓመት በሠናይ ክብር ማዕከለ ብዙኃን ይመውት።

 

      ፈ ፯፻፤ ብሂል፤ ፈካሬ ምሥጢራት ጥዑመ ቃል ወልሳን የዋህ ሰብእናሁ በእንተ የውሃቱ ያፈቅርዎ ኵሎኡ ሰብእ ወእዝማዲሁ ይትፌሥሑ ቦቱ እምድኅረ ልሕቅ ያጠሪ ብዙኃ ንዋየ በሢመት ቤተ ክርስቲያን የሃንጽ ወያስተጋብእ ሎሙ ኵሎ ነገር ለነገሥት ወለመኳንንት ኵሎሙ ቅሩባኒሁ ያፈቅርዎ ወዘርሑቅ የሓምይዎ ወእምድኅረዝ ያወስብ ብእሲተ ኅሪተ ወይወልድ ባቍዐ ዘይረብሖ በኵሉ ይበቍዓ ለነፍሱ በሠናይ ምግባሩ ይወርስ ርስተ አቡሁ ወአልቦ ዘይመውዖ በመዋዕሊሁ በልቡ ሕዳጥ ኃዘን ኢየኃጥእ ወኵሎ መዋዕለ ዘመኑ ፹ወ፰ ዓመት ውእቱ።

 

      ፐ ፰፻፤ ብሂል ፐፒረላይ ቀይሕ ለይ የዋህ ወንጹሕ ብእሲ ውእቱ ይኤድም ላህዩ ፀምሩ ሠናይ ወቆሙ ነዊሕ ካህነ ሠናየ ይከውን ወያስተምህር ለሕዝብ ያፈቅር ለአዝማዲሁ ወለኵሉ ሰብእ ሕማመ ዓይን ያፈርሖ በብእሲቱ ይትፌሣሕ ወበውሉዱ የኃዝን ይሜንንዎ ደቂቁ ኢይነዲ ወኢይብዕል ሕማመ ልብ ወሰዓል ቦቱ ያፈቅር ግብረ ጥበብ ብዙኅ እክል ይከውን ሎቱ በጊዜ ምንዳቤ ጠቢብ ወተዓጋሢ ውእቱ ወይከውን ዕድሜሁ ፰ ወ፮ ዓመተ በተፊአ ደም መዊት ያፈርሆ።

 

                          50

 

                   ፪ኛ ሓሳበ ፍኖት።

 

ስም ወእም ወንጌላዊ ወርኅ ዕለት በ፲፪ ግደፍ።

 

      ፩፤ ለእመ ወዳእከ በሌሊት ሠናይ ሕልመ ትሬኢ በሓመር ፈረስ የተቀመጠ ዓይነ ጐረጥ ሰው ታገኛለህ ሙሽራ ታገኛለህ ነገርህ ይቀናሃል። ፪፤ መንገድ የሚሄዱ ሰዎች ታገኛለህ ጉሽ ጠላ ትጠጣለህ ነገርህ ይቀናሃል ምልክቱ በመንገድህ የተጣላ ሰው ታገኛለህና ታስታርቃለህ። ፫፤ ኢትሑር መንገደ እኩይ ውእቱ ገንዘብህ ይጠፋብሃል ከሰው ትጣለለህ ወደዘመቻ የሄድህ እንደሆነ ትወጋለህ (ትቆስላለህ) ባለንጀራህ ይሞታል ብትገድልም ምርኮ ያገኝሃል ተጠበቅ ብትቀር ይሻልሃል። ፬፤ በህልም ሢሣይ ታያለህ በመንገድህ እልልታ ጭፈራ ትሰማለህ ከውድማ እሣት ታያለህ ዜና ሞት ትሰማለህ ሰው ይጣላና ትገላግላለህ ከዘመቻ ከብት ታገኛለህ የምትወደውንም ሰው ታገኛለህ ነገርህ ይቀናሃል። ፭፤ ከዘር ውላጅና ከባለጋራህ ጋር በሕልም ትከራከራለህ ወደ አደባባይ ብትወጣም ነገርህ አይቀናህም በሁሉም ዘንድ ፍቅር ይጐድልብሃል አይቀናህም። ወደዘመቻም ብትሔድ ሳይቀናህ ትመለሳለህ ምልክቱንም ባለንጀራህ የሰው ከብት ሰርቆ ሲነዳ ትጣላለህ አውሬ ያስደንግጥሃል ካደርክበት ቤት ጥል ትሰማለህ። ፮፤ ከቤትህ ስትነሣ ጭቅጭቅ ይነሣብሃል መንገድህን በኃዘን ትጀምራለህ ወደዘመቻ ብትሔድ የሰው ከብት አታቀላቅል ካንተ ጋር ያለ ሰው ይወድቅብሃል በሽተኛ ይዘህ ትመለሳሰህ በዘመትህበትም ቦታ አይቀናህም መቅረት ይሻልሃል ከመንገድ ስትደርስ ታላቅ ወሬ ትሰማለህ። ፯፤ በሕልምህ ስትመገብና ደስ ሲልህ ታድራለህ ያየኸው ሕልም ገሚሱ ይጠፋብሃል ከመንገድ ስትደርስ ታላቅ ወሬ ትሰማለህ ምልክቱ እራቁቱን የሆነ እብድ ታገኛለህ የሴትም ይሁን የወንድ ለቅሶ ትሰማለህ። ፰ ሰናይ ቅቤ የተቀባ ሎቴ ወይም ሠሪቴ የሻጠ ወይም እንደጊዜው ያጌጠ ሰው ታገኛለህ ፍሥሓ ነው። ፱፡ ፲፡፲፩፤ ከምታድርበት አጠገብ የብር መደብር አለ ኃዘነተኛ ከል የለበሰ ታገኛለህ ወደ ዘመቻ ወደ ዘመቻ ወደ ጉዳይህም ብትሄድ ይቀናሃል ወኵሉ ፍሥሓ። ፲፪፤ በነግህ ተነሣ አብሮህ የሚሄድ ሰው ታሞ ይመለሳል ጥቂት ገንዘብ ወድቆ ታገኛለህ ዝናም ይመታሃል ንግድም ብትሄድ ይቀናሃል ፍሥሓ በኩሉ።

 

           

                          51

 

            ሓሳበ ክዋኔ ኵሉ ነገር፤ በ፲፱ ግደፍ።

 

      ፩፤ ፍጡነ ጥፍኣት። ፪፤ ነቢብ ወዓመፃ። ፫፤ ደዌ ወትንሣኤ። ፬፤ ሕማም ወትካዜ። ፭፤ ሕማመ ሥራይ። ፮፤ ደዌ ልብ።  ፯፤ በዘመከረ ይጠፍእ። ፰፤ ብዕል ወፍሥሓ። ፱፤ ኃዘን ወገዓር። ፲፤ ገዓር በሕሊና ፲፩፤ ስሕተት ወጌጋይ። ፲፪፤ ደዌ ዓይን ንዋየ ባዕድ ደረክብ። ፲፫፤ ስሕተት ወጌጋይ ትረክብ ተሃየይ እምኵሉ። ፲፬፤ በንዋየ ባዕድ ይከብር ደም ያፈርሖ። ፲፭፤ ከዒወ ደም። ፲፮፤ ጽጋብ ወፍሥሓ። ፲፯፤ ድንጋፄ በሞት። ፲፰፤ በኵሉ ነገር ድንጋፄ። ፲፱፤ በእንግዳ ትቴክዝ።

 

                          52

 

                   ፫ኛ ሓሳበ ሕሙመ።

 

      ስም ወስመ እም በ፲፫ ግደፍ። ፩፤ ይትረኃው መቃብሩ እስከ ሳብዕ። ፪፤ ኀበ ዓቃቤ ሥራይ ይሑር የሕዩ ሥራየ አንስት ሀሎ በከርሡ በ፱ ወርኅ ይመውት። ፫፡፬፤ ብዙኅ የሐምም የሐዩ። ፭፤ ወላጅ ጋኔን ይጻረሮ ጥምቀት ወመፍትሔ። ፮፤ ከማሁ ከርቤ ተዓጠን የሐዩ።፯፤ ሥራየ አንስት ሀሎ ብሔረ ባዕድ፤ ኢይሑር እምነ ቤቱ በሌሊት አውጽእዎ ይመውት። ፰ ሥራይ ይፈርሆ ሆሣዕና ይከማሁ። ፲፩፤ ሰአል ወጸሊ ኅበ እግዚአብሔር ዓቢይ ኃዘን። ፲፪፡፲፫፤ ጽኑዕ ነገር ሀሎ ተዓቀብ እምዓመት እስከ ዓመት በበወርኁ ግበር ጭዳ።

 

                          53

 

                      ጌራ መዊእ።

 

      ስላም ለዝክረ ስምከ ትግምርተ አናብስት ዘቦ። ወለመዓትከ ዓዲ ንጥረ መባርቅት ዘኢይትሔዘቦ። ጌራ መዊእ ኃያል ለክብረ መንግሥት ዘይትዓቀቦ። ከዐው በላዕሌሆሙ ፈለገ እሳት በገቦ። ለአፅራረ ንጉሥ ዘበሰይፍ አንጠብጥቦ። ሰላም ለስእርተ ርእስከ ነበልባለ እሳት አምሳሉ። ወኅብረ መብረቅ መፍርህ ዘያበርህ ሥነ ፀዳሉ። ጌራ መዊሕ ዕሳት ለእግዚአብሔር ሠርጉ አክሊሉ። ክልኦሙ ለአፅራርየ ለሰይፍከ በነበልባሉ። ወኢታዕርፎሙ ውስተ ምድር ኢይብቍሉ። ሰላም ለርእስከ ሰርፈ ነበልባል ዘዓገቶ። ወለገጽከ መብረቅ መገሥጸ ፀር ከንቶ።  ጌራ መዊእ ኵለሄ ለእግዚአብሔር ዘተአኵቶ። ሰይፍከ ነበልባላዊ እንዘ ይሬኢ እሳቶ። ፈነዎ ለነጉሥ ይቅትል ጸላእቶ። ሰላም ለቀራንብቲከ ትእይንተ ንጉሥ ዘየዓቅባ። ወለአዕይንቲከ ሰላም ምስለ አፈጽባሕ የበባ። ጌራ መዊእ መብረቅ ለእሳተ ሕይወት ሀንባባ። ደምስሶሙ ለአፅራርየ ለእመትከ በላህባ። በሓፀ መላእክት ተቀሥፉ ለኦሪት ሕዝባ። ሰላም ለአእዛኒከ እለ ይሰምዓ ትእዛዞ። ለእሳተ ሰማይ ጊዜ ተሓውዞ። ጌራ መዊእ ናዛዚ ለሕዝቅያስ ዘትናዝዞ። በኵናትከ ነበልባላዊ ለገበዋቲሁ ርግዞ። ወለፀረ ዓመፃ በእሳት ግንዞ። ሰላም ለመላትሒከ እለ ፄነዋ መዓተ። ለረዲአምንዱብ ሕዝቅያስ ጊዜ ትመልሕ አስይፍተ። ጌራ መዊእ ገሥፅ እለ ከዓው እሳተ። አስጥሞሙ በባሕረ እሳት ለእመ ተንሥኡ ግብተ። ሓራ ፀረ ንጉሥ ኃይል ለይኩን መሬተ። ሰላም ለአፅናፊከ ምዑዘ ፄና እምርሑቅ። ወለከናፍሪከ ዘነበበ ምሥጢረ መለኮት ረቂቅ። ጌራ መዊእ በረድ ወጌራ መዊእ መብረቅ።  ምላሕ እግዚኦ ሰይፈ መውእ ምውቅ። ለዕለ ፀረ ንጉሥ በማዕከሉ ይደቅ። ሰላም ለአፉከ አፈ መንፈስ ቅዱስ ዘጥዕሞ። በሓፀ ረድኤት እሳት በትዕግሥት ወበአርምሞ። ጌራ መዊእ ምላሕ ሰይፈከ ጊዜ ተሓትሞ። ሰናክሬም ዓላዊ ውስተ ባሕረ መቅሠፍት ተሰጥሞ። ሓፀ መዓትከ ፈኑ ላዕለ ፀር ከመ ይክዓው ደሞ። ሰላም ለአስናኪከ እለ ይሥሕቃ በፍሥሓ። ወለልሳንከ ርቱዕ ለግፉዓነ ሞት ዘይፈትሓ። ጌራ መዊእ ሚጢኒ መንገለ ሀሎ ፍሥሓ። ገሥዖሙ ለአፅራ ርየ በእሳተ መዓት አሜሃ። ከመ ተሓትም ምድር ወታብቁ አፉሀ። ሰላም ለቃልከ ንባበ መለኮት ነዳዲ። ዘነፍሐ እሳተ በእስትንፋስከ ዓዲ። ጌራ መዊዕ ሌሊተ ቅድመ ፈጣሪ ሳጋዲ። ምሕረትከ በላዕሌየ እግዚኦ ኢታጐንዲ። ከመ የሓቅፎ ለወልዱ ወላዲ። ሰላም ለጕርዔከ ጕርዔ ነበልባል ወፍሕም። ለክሣድከ ሥርግው በባዝግና መለኮት ኤዶም። ጌራ መዊእ መግረሪ ወጌራ መዊእ መስጥም። ምላሕ ሰይፈ መዓትከ ከመ ፀረ ንጉሥ ትልጉም። ትርድአኒ ነዓ በነዋሕ ዓም። ሰላም ለመትከፍትከ ፀዋሬ መለኮት መዋኢ ወለአክናፊከ አርእስተ ፀር ወጸላኢ። ጌራ መዊእ የዋህ ለገፋዓነ ፈረስ ረዳኢ። ቅስፎሙ ለዕድዋንየ እንዘ ግፉዓነ ትሬኢ። ቅድመ ፀረ ንጉሥ ኃያል ይትኃፈር ገፋዒ። ሰላም ለዘባንከ መብረቀ እሳት ግልባቤሁ። ወለእንግድአከ ዘፆረ እሳተ መለኮት ዲቤሁ። ጌራ መዊእ ቅውም ለእግዚአብሔር ቅድሜሁ። ቅስፎሙ ለዕድዋን ሶበ ወውዑ ወከልሑ። እንዘ ሰይፈ እሳት ለከ አእዳው ይምልሑ። ሰላም ለሕፅንከ ሐፅነ መንፈስ ቅዱስ ዘተባየጾ። ወለአእዳዊከ ዘመልሓ ሰይፈ መሓፒል ለተጋይጾ። ጌራ መዊእ መምሕር ለመልአከ ሞት ዘትጌሥጾ አረሚ ዕድውየ ለዘመድ ዐመጾ። ሰላም ለመዛርኢከ ከመ ቀስተ ብርት እለ ኃየላ። ወለኵርናዕከ ክቡድ ለቀትለ አፅራር ተኵላ። ጌራ መዊእ እሳት ለሓመልማለ ኖኅ ዘትኬልላ። ፈኑ ሊተ እንግዚኦ ሰይፈ ነበልባል በኵላ። እስከ አመ ይመጽእ ለሰብእ ለኦሪት ቃላ። ሰላም ለእመትከ መሓፒለ እሳት ሙጻኡ። ወለእራኅከ ዓዲ ምስለ ሰይፈ እሳት ካልኡ። ጌራ መዊእ እሙር ለሊቀ መላእክት ሳብዑ። አሕዛበ ምድር ሶበ ላዕሌየ ተንሥኡ። ፈኑ ላዕሌሆሙ ሰይፈ ሞት ይብልዑ። ሰላም ለአፃብዒከ እለ ተረሰዩ ነበልባለ። ወለአጽፋረ እዴከ ልሁያት በክንፈ መባርቅርት ዘአጥለለ። ጌራ መዊእ በነሥኤ ሠርጎ አዕዳው ኃይለ። ሀቦሙ ወክልኦሙ ለአፅራረ ዚአየ ቀትለ። አው ሊተ ለዕድዋን በገንጢኖስ አንሓለ። ሰላም ለገቦከ ለፌ ወለፌ መሓፒሉ። ወለከርሥከ ዓዲ ዘፈልፈለ እሳተ ፈልፈሉ። ጌራ መዊዕ እሳት ዘቅድመ አምላክ ትሄሉ። ብከ ዘይትዌከሉ በነገረ ትፍሥሕት የሃሉ። ወአፅራረ ንጉሥ ይደምሰሱ ወመሬተ ይምሰሉ። ሰላም ለልብከ እሳተ መለኮት ምክሩ። ወለሕሊናከ ርቱዕ ሓልዮ ሠናያት በውስተ ዝክሩ። ጌራ  መዊእ ቀዋሚ ለእግዚአብሔር ንጉሥ መንበሩ።ይትኃፈሩ ወይኅሠሩ ሠራዊተ ቤልሆር ፀሩ። አክናፈ ነድ ሥልጣኑሙ ዝሩ። ሰላም ለሕንብርትከ ሕንብርተ እሳት ገሣፂ። ወለሓቌከ ቅኑት ሰይፈ ነበልባል መያፂ። ጌራ መዊእ ነፋስ ለረድኤተ ሰብእ ረዋጺ። አኮኑ አንተ በረድኤተ ንጉሥ ሓዋጺ። በሰይፈ እሳት ግሩም ይትኃፈር ዓማፂ። ሰላም ለአቍያጺከ አዕማደ ወርቅ ወጰንደጢን ወለአብራኪከ ሰጊደ እለ አውተራ  በይምን። ጌራ መዊእ መምሕር ቀናተ ነበልባል ዘቀርሜሎን። ስድዶሙ ለአፅራርየ እለ ውስጠ ኵሉ መካን። በሰይፈ  እሳት በሊሕ ለዘፋርስ ወሜዶን። ሰላም ለአእጋሪከ ዘጸፍጸፈ እሳት ምቅዋሙ። ወለሰኳንዊከ መብረቅ ዘኅብረ  ነበልባል መቅድሙ። ጌራ መዊእ ገሥጽ ትእይንተ ንጉሥ ኵሎሙ። ከዓው እግዚኦ ፈለገ እሳት በዓቅሙ። ላዕለ ዕድዋንየ በእሳት ይሕምሙ። ሰላም ለመከየድከ ዘተረሰየ ስብሓተ። ወለአፃብዒከ ርሱያት በዓጽቀ ነበልባል ዘተአኵተ። ጌራ መዊእ  ገሣፂ ዘበኃይለ መንፈስ ግብተ። አስተኃፍር ጸላእትየ አኮኑ ይኩኑ መሬተ። እስመ ሊቀ ካህናት ንጹሕ ወጻድቅ አንተ። ሰላም ለአጽፋር እግርካ እለ ተገልፋ ከመ መብረቅ። ወለቆምከ አዳም ዘኅብረ ነበልባል ምውቅ። ጌራ መዊእ የዋህ ሓዋጼ ጻድቃን አዕፁቅ። ኃይለ ትንሣኤ ፀር አመ ተሰምዓ በጽድቅ። ከመ ትዝርዎሙ ነዓ ለአፅራር ደቂቅ። ሰላም ለመልክዕከ እመልክዓ መልአክ ክቡር። ዘይሤኒ ኅብሩ ከመ ዕንቈ ጳዝንዮ ጶዴር። ጌራ መዊእ ኃያል ወመግረሬ ፀር። ዝርዎሙ ለአፅራርየ መንገለ ቀልቀል ወባሕር። ወከመ ነፋስ ይዘረው በኃሣር። ኦአምላከ ጌራ መዊዕ ዕቀበኒ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ለገ። 

 

 

      ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ወውእቱ ቃል ቃለ እግዚአብሔ ኃያል ስፍያድ ፩ አብ ቅዱስ አድናኤል ቀዳሚሁ ውእቱ ወውእቱ ቃል ቃለ እግዚአብሔር ሕያው ናምሩድ ፩ ወልድ ቅዱስ ዐማኑኤል ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ወውእቱ ቃለ እግዚአብሔር ጽኑዕ ሱሐል ሱሐል ፩ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ጰራቅሎጦስ ሙራኤል በዝ ስምከ ወበኃይለ ዝንቱ ጽምረተ ሥላሴ በከመ ወሃብኮሙ ሥልጣነ ለእለ የአምኑ ብከ በከመ አስተጻመርኮሙ ለአብርሃም ወለሣራ ወለኵሎሙ ሰብእ ፍቁራኒከ በዝ ስምከ መንፈስ ቅዱስ ወበኃይለ መስቀልከ ሆሣዕና ዓለም ክርስቶስ ሀበኒ ሞገሰ ወሥልጣነ በኀበ ኵሊ ሰብእ አስተፋቅረኒ ወአስተጻምረኒ ምስለ ኵሎሙ ሰብእ ከመ የሀቡኒ ንዋየ ወኵሉ መፍቀደ ልብየ ወይስግዱ ታሕተ እገርየ ሊተ ለገብርከ።

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ብርሃናኤል አጉዳ አግፍላላኤል ዘንተ አስማተ ዘወሀቦሙ እግዚአብሔር ለአናንያ ወአዛርያ ወሚሳኤል እንዘ ይትናገሮሙ ሚካኤል ቀዊሞ ማእከለ  እቶነ እሳት ወአማዕተበ በትሮ ኀበ ፫ቲሆሙ ዘንተ አስማተ ዘ፴ወ፱፻፲ወ፱ ወሶበ ይትናገር ሚካኤል ዘንተ አስማተ ወ፫ ደቂቅ በውስተ እቶን ቈረ ወኮነ ጠለ ወዓውሎ። ነፀረ ወርእየ ናብከደነፆር ንጉሥ ወይቤ ፫ተ እደወ ፈነውነ ወወደይነ ማዕከለ እሳት ዘይነድድ ፫ተ ዕለተ ወ፫ ለያልየ ወርኢኩ ፬ተ እንደወ ወራብዖሙሰ ወልደ እግዚአብሔር ይመስል ወምስለዝ ኮነ ትንቢት አመ ይትወለድ ክርስቶስ እግዚእነወጸሐፉ ጠቢባን ዘንተ አስማተ አእሚሮሙ ከመ ይድኃኑ እምንዳድ ወእምነቀጥቃጥ ለእመ ተጠምቁ በማይይድኅኑ በዝንቱ አስማተ እግዚአብሔር ለእመ ጸሐፍከ ኀበ ጽላተ ብርት ወትሰቅሎ ኀበ ዓምደ ቤትከ እመብረቅ ወእሳት ወሶበ ውዕየ እሳት ትነሥእ ዘንተ ወታነብብ ላዕለ አንቆቅሖ ወትቀብዖ ወተሀዩ በስመ እግዚእነ አሜን።

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ፩ አምላክ አልፋወዖ ፫ አልፋ ድልጣ ወቤጣ ወበቃለ የውጣ አመዛርጣ ፫ ድቡጣ ኪርያላይሶን እብኖዲ ታኦስ አዝዮስ ኪራያላይሶን እብኖዲ ታኦስ አዝዮስ ማስያስ አኽያ ሸራኽያ ኤልሻዳይ ጸበኦት ዐማኑኤል ኦእግዚ እየ አየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ወወልደ ማርያም ሥግው ዐማኑኤል አምላኪየ ንጉሠ ስብሐት ወሀቤ ኵሎን ንዋያት እስመ ሔር አንት ወመፍቀሬ ሰብእ ወኵሉ ይትከሐለከ በዝ ቃለ መለኮትከ ተማኅፀንኩ ከመ ተሀበኒ ብዕለ ወሞገሰ ክበ ወሥልጣነ ጸጋ ዘኢይማስን በኅበ ኵሉ በከመ ተሰቀልከ ማዕከለ ፪ ፈያት ወከዓውከ ደመ ክቡረ ዲበ ዕፀ መስቀል ቅዱስ ከመ ይኩነነ ለነ መብልዐ ጽድቅ ወስቴ ሕይወት ዘበአማን አንተ ውእቱ  ቃለ እግዚአብሔር ኃያል አዶናይ ጸባዖት በከመ ነሥኡከ ወሰለቡከ አልባሲከ ወአልበሱከ ከለሜዳ ዘለይ ወተካፈሉ ለእርሶሙ ጸላእትከ አንተ ውእቱ ቃለ እግዚአብሔር ኃያል ዘትመልዕ ለኵሉ አኽያ ሸራ ኽያ በራኽያ እስእለከ እግዚኦ አምላኪየ ከመ ተሀበኒ ተምኔትየ ኵሎ አሚረ ወአዝዞሙ ለኵሎሙ እድ ወአንስት ከመ የሀቡኒ ንዋዮሙ ወይፍትሑ እደዊሆሙ በፍቅረ ዚአየ አንተ ውእቱ ቃለ እግዚአብሔር ኃያል ወግሩም ሢሳየ ነዳያን ወተስፋ ቅቡጻን። ዐማኑኤል አምላኪየ በከመ ሰሀቡከ በሓብል አይሁድ ዓማፅያን ወተጸፋዕከ አንተ በፍቅረ ሰብእ ኦ ዘሖርከ በዝ ኵሉ ወበኃይለ አስማቲከ ተማኅፀንኩ ከማሁ ስቅል ወከዓው ልቦሙ ለኵሎሙ ሰብአ ሃገር ወትእይንት በፍቅረ ዚአየ በኃይለ ዝንቱ አስማቲከ ንሣእ ወክፍል ልቦሙ በፍቅረ ዚአየ ለኵሎሙ እድ ወአንስት ወስልብ ልቦሙ ወፅፋዕ እዝኖሙ በፍቅረ ዚአየ ለኵሎሙ እድ ወአንስት ከመ የሀቡኒ ንዋየሙ በዛቲ ዕለት። አንተ ውእቱ ቃለ እግዚአብሔር ኃያል ወማኅየዊኦ ክርስቶስ ዐማኑኤል አምላኪየ ወአምላክ ኵሉ ፍጥረት በከመ አድለቅለቀት ምድር ወተሀውከት ኢየሩሳሌም ጸልመ ፀሐይ ወወርኅ ደመ ኮነ በጊዜ ሞትከ ወእምብዝኃ መንግሥትከ በዝንቱ ኵሉ ሕማማተ መስቀልከ እግዚአብሔር አምላኪየ ተማኅጸንኩ ብከ። ከማሁ ድፍን ወአጽልም አዕንይተ ልቦሙ በፍቅረ ዚአየ ወአሙት ኵለንታሆሙ በጣዕመ ነገርየ በኃይለ ዝንቱ አስማቲክ እግዚአብሔር አድለቅልቅ ወአስተሐውክ ልቦሙ ተሐውክ ወአስተሐምም ሕሊና ሥጋሆኡ በፍቅረ ዚአየ ለኵሎሙ ሰብእ ወአንስት። ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ ወአብጽሖ እስከ ለሞት ፅፅዱት ወብርህት እንተ ትትመረጐዝ በወልድ እኁሃ እምኀበ ኮል አንሣእኩከ በህየ ሐመት ብከ ወላዲትከ አንብረኒ ከመ ኅልቀት ውስተ ልብከ ወከመ ማዕተብ በመዝራዕትከ እስመ ፍቅር ከመ ሞት ጽንዕት ወድርክት ከመ ሲኦል ቅንአት ክነፊሃ ክንፈ እሳት ላህባ ማይ ብዙኀ ኢይክል አጥፍኦታ ለፍቅር ወአፍላግኒ ኢያንቀለቅልዋ እመ ወሀበ ብእሲ ኵሎ ንብረቶ ለፍቅር ከማሁ ሀበኒ ሞገሰ ወሥልጣነ በኀበ ኵሉ ትውልደ ዕጓለ እመሕያው ወአስተፋቅረኒ ምስለ ኵሉ ደቂቀ አዳም ከመ የሀቡኒ ንዋየ ወኵሎ መፍቅደ ልብየ ወይስግዱ በብረኪሆሙ ታሕተ እገርየ ኵሎሙ ሰብእ ሊተ ለገብርከ።

 

                          54

 

             ጸሎተ መስተፋቅር ወመግረሬ ፀር

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ነገረ መስተራትዕ ዘወሀቦ እግዚአብሔር ለዮሐንስ ፍቁሩ ወይቤሎ፤ ቱላንዳ ፈኑ ሊተ መላእክተ እግዚአብሔር ከመ ይኩኑ ምስሌየ መዓልተ ወሌሊተ በየማንየ ወበጸጋምየ በቅድሜየ ወበድኅሬየ  አስተፋቅረኒ ምስለ እለ ይትበአሱኒ ሊተ ለገብርከ ወርእየ እግዚአብሔር ፈጣሪየ ወነጸረ ወይቤላ ሑሪ ወተፋቀሪ ምስለ ኵሎሙ ፍቁራንየ ሥዩማን መላእክትየ ወምስለ አዳም ገብርየ ወምስለ ኵሎሙ ዘርዐ እስራኤል ትውጽእ ቅድስት ድንግል ማርያም እንተ ማኅደርየ ርእያ ከማሃ ረስየኒ ማኅደረ መንፈስ ቅዱስ ሊተ ለገብርከ…… አብ በራፎን መንጦላዕተ ምሥጢርከ ወምስለ ሥዩማን መላእቲከ አስተፋቅረኒ ምስለ እለ ይትበአሱኒ ሊተ ለገብርከ …….. በከመ አስተፋቅርካ ለማርያም እምከ ከማሁ አስተፋቅረኒ ሊተ ለገብርከ ……. በከመ አስተፋቀርኮሙ ለ፳ ወ፱ ካህናተ ሰማይ ከማሆኑ አስተፋቅረኒ ሊተ ለገብርከ …… በከመ አስተፋቅርኮሙ ለ፬ እንስሳ ከማሁ አስተፋቅረኒ ለተ ለገብርከ …… በከመ አስተፋቀርኮሙ ለሚካኤል ወገብርኤል ሊቃነ መላእክቲከ ከማሆኑ አስተፋቅረኒ ምስለ እለ ይትበአሱኒ ሊተ ለገብርከ …… በከመ አስተፋቀርኮሙ ለ፲ ወ፪ ሐዋርያት ከማሆኑ አስተፋቅረኒ ሊተ ለገብርከ …… በከመ አስተፋቀርኩሙ ለ፸ ወ፪ አርድእተ ከማሆሙ አስተፋቅረኒ ሊተ ለገብርከከ……. በከመ አስተፋቀርኮሙ ለካህናት ወለዲያቆናት ከማሆሙ አስተፋቅረኒ ሊተ ለገብርከ……. በነጐድጓድኤል፤ በነጐድጓድኤል። በነጐድጓድኤል፤ ስምከ ሀበኒ ክብረ ወሞገሰ ምስለ ነገሥት ወመኳንንት ሕዝብ ወአሕዛብ ምስለ አግብርት ወአእማት ምስለ ደቂቅ ወሕፃናት አስተፋቅረኒ ሊተ ለገብረከ…… በከመ አስተፋቀርኮሙ ለ፳ ወ፪ ፻፻ መላእክት እለ ይቀውሙ ውስተ ዓውደ መንበሩ እንዘ ይብሉ ቅዱስ፤ቅዱስ፤ቅዱስ፤ እግዚአብሔር ጸባዖት ፍጹም ምሉእ ሰማያተ ወምድረ ቅድሳተ ስብሐቲከ ለቢሶሙ ልብሰ እሳት ተገልቢቦሙ በንጥረ መባርቅት ከማሁ አልብሰኒ ሞገሰ ሊተ ለገብርከ………ቅሰራም፤ ቅሰራም፤ ቅሰራም፤ በኮሬብ፤በኮሬብ፤በኮሬብ፤ በኮከበ፤ ምሥራቅ በኮከበ ምዕራብ በኮከበ ሰሜን፤ በኮከበ ደቡብ፤ ድርማ ድርማ፤ድርማ፤ ወበስምከ አብድኅሰ አዮጊ ወበስመ መልአክ መልአክኤል፤መልአክኤል፤ መልአክኤል መሐካኤል መሐካኤል ፤ አዲራእል፤ ከዲራኤል፤ ድንቃስ አንቅሕ ልቡናሁ ወአእምሮ ሕሊናሁ ለገብርከ…….ወድፍኖሙ ለኵሎሙ ፀርየ ወፀላእ ትየ ሊተ ለገብርከ…….ተማኅፀንኩ፤ በአስማተ ደርያም በቶሳቲቱ ተተተተደቡ ዕቀብ ነፍስየ ወሥጋየ ኦእግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዐጾከ ቀላያተ ወሐተ ምከ ግሩመ። ከማሁ ኅትም አፋሆሙ ወዕፁ ጕርዔሆሙ ወአውግዞሙ በውግዘተ ጴጥሮስ ወጳውሎስ አርእስተ ሐዋርያት በኅቡዕ ስሙ ለእግዚአብሔር በ፭፻፼ ሰና ስለ እሳት ፭፻፼ ሰጐንፕረ እሳት ፭፻፼መሐፒለ እሳት ፭፻፼ መኵርበ እሳት እስር ልሳኖሙ ወዕጹ ጕርዔሆሙ ወኅትም አፋሆሙ ለፀርየ ወለፀላእትየ አድኅን ርእስየ ሊተ ለገብርከ…..ተማኅፀንኩ በበትረ ሢመቱ  ለሚካኤል ሊቀ መላእክት ወበገብርኤልዜናዌ ትፍሥት ተማኅፀንኩ በደብረ ጽዮን ጽርሐ መንግሥቱ ወበከመ አፍቀርኮመ ለሚካኤል ወገብርኤል ሊቃነ መላእክቲከ ከማሆሙ አክብረኒ ወአልፅለኒ በቅድሜከ ወበቅድመ ውሉደ አዳም ወሔዋን ሊተ ለገብርከ……ተማኅፀንኩ በቅድመ መንበሩ ለእግዚአብሔር ፈጣሬ ሰማያት ወምድር ወበኅቡዕ ስሙ ለእግዚአብሔር ዘኢይትነገር ወዘኢይትዓወቅ ወዘኢይትከሠት ተማኅፀንኩ አልዑድ ድብድድብ ዘተፅነ በላዕለ ነፋሳት ወመባርቅት በ፪፻፼   ድንጓፄል እለዕነ ፷ የአቅብዎ መላእክት ዘእሳት ተማኅፀንኩ በኪሩቤል መንበሩ የልሁድ ምድባሁ መተማኅፀንኩ አነ ገብርከ……አውላካኤል መደንግጽ አምላክ ከማሁ አደንግጾሙ ለፀርየ ወጸላእትየ አዝሩኤል አካክኤል ወአንክሩያኤል ቶርኤል ትርትርያኤል ፍጽም አፋሆሙ እስከ ይከውኑ በሐመ ወብዑድ ወስኩረ። በስመ ሥሉስ ቅዱስ ፩ አምላክ አእደ ኢድዩታልዋዎ አቤግያውያን ጸላያንያት አኦች ንትያሸ ንያች ያርሸንያ ያመሽችፋትልያ በኃይለ ዝንቱ አስማቲከ አድኅነኒ ሊተ ገብርከ……

 

 

    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ቱላዳን ቱላዳን ቱላዳን በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ በስመ እግዚአብሔር ወልድ ዋኅድ በስመ አብ ወበስመ ወልድ ወበስመ መንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ቱላዳን ተፈጥሩ መላእክት ከመ ይትለአኩ ውስተ ገጸ ኵሉ መካን ወአነሂ ጸዋዕኩክሙ ወእቤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ቱላዳን በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ቈኃት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ቍልቈይ ዘገበርክሙ አትኩኒ ምስሌየ መዓልተ ወሌሊተ በየማንየ ወበፀጋምየ በቅድሜየ ወበድኅሬየ ወአስተፋቅሩኒ ምስለ እለይትበአሱኒ ሊተ ለገብርክሙ……..

 

     

                          55

 

              ጸሎት በእንተ መፍትሔ ሃብት።

 

     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ጸሎት በእንተ መፍትሔ ሃብት ወግርንማ ወጸሎተ ድንጋፄ አአትብ ገጽየ ወኵለንታየ በትእምርተ መስቀል በስመ ሥላሴ በእንተ ማዕሠረ አጋንንት ወሰይጣናት ወግርማ ሞገስ ከመ አቡነ ዳዊት ወሰሎሞን በርሃ፣ በርሃ፣ በርሃ፣ በርሃ፣ በርሃ፣ በርሃ፣ጨ፣ጨ፣ጨ፣ጨ፣ጨ፣ጨ፣ሟ፣ሟ፣ሟ፣ሟ፣ሟ፣ሟ፣ሟ፣ዮ፣ዮ፣ዮ፣ዮ፣ዮ፣ዮ፣ዮ፣ ገይሙት፣ገይሙት፣ገይሙት፣ ያጥብሐል ፯፣ፌ፣፯ ዮፍታሔ በዝንቱ ግብርከ ወበኃይለ ዝንቱ አስማቲክ ፍታሕ ማዕሰረ እደዊሆሙ ወአራኅርኅ ሕሊና ልቦሙ ወአደነግጽ ልቡናህሙ ለሰብአ ሀገር ወየሀቡኒ ሃብተ ወፈኑ ዘየዓቅቡኒ መላእክት መፍቅደ ልብየ ሊተ ለገብርክ……. ፩ አብ ቅዱስ ሰንተው ቀንተው ቀርነው ቀርነለው ሙራኤል ኃይለ ግርማሁ እሳት ወሞገሰ ፍቅሩ ጽኑዕ ወጣዕመ ነገሩ ምሉእ ወሣዕሣዐ አፋሁ ጥጡሕ በእግዚአብሔር  አብ ንጉሠ ሰማያት ወምድር ዘይሁብ ሲሣየ ለኵሉ ዘሥጋ። ኃይለ መስቀሉ ክቡር ወፍቅረ ጸጋሁ ዓቢይ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ አድናኤል አድናኤል አድናኤል። ኢያኤል ኢያኤል ኢያኤል አስብኤል አስብኤል አስብኤል በእሉ አስማተ ቃልከ ተማኀፀንኩ መልአከ ሜምሮስ ደቡባዊ ነፋስ ኃይለ ድብ ንጉሥ ወቃለ እግዚአብሔር ኃያል መንፈስ ቅዱሳ ሀበኒ እግዚኦ ኃየለ ወሥልጣነ ፍቅረ ወሞገሰ ወሰላመ ቅደመ ፀርየ ወጸላእትየ።ወበቅድመ ነገሥት ወመኳንንት ከመ የሀቡኒ ንዋየ ዬ፣ዬ፣ዬ፣ ፍታሕ ማዕሠረ እመዊሆሙ ወአራኅርኅ ሕሊና ልቦሙ ሊተ ለገብርከ………. መልአክ ሜምሮስ ደቡባዊ ንጉሥ ደቡባዊ ነፋስ ኃይለ ድብ ንጉሥ ፩ ወልድ ቅዱስ ሰንተው ቀንተው ቀርነው ቀርነለው ምናቴር ኃየለ ግርማሁ መርዕድ ወሞገሰ ስሙ ዘያስተፌሥሕ ለትውልደ ትውልድ ወጣዕመ ከናፍሪሁ ሐሊብ ዘይትፈቀር እመዓር ወሦከር ወሣዕሣዐ አፋሁ ዘያጸግብ ለኵሉ ዓለም ወስብሐተ ስሙ ለአምላከ ሰማይ ወምድር ዘይነግሥ ለቤተ ያዕቆብ ለዓለም። ትእምርተ መስቀሉ ወነገረ ጥበቡ ወፍቅረ ሰላሙ ለእግዚብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ታዖስ፣ ታዖስ፣ታዖስ አዝዮስ ፫ ማስያስ ፫ ሔጥ ፫ ሱሐል ፫ ግርማኤል ፫ አማሩኤል ፫ ዐማኑኤል ፫ አምላኪየ ሀበኒ እግዚኦ ኃይለ ወሥልጣነ። ግርማ ወሞገሰ በቅድመ ፀርየ ወጸላእትየ ወበቅድመ ኵሎሙ እድ ወአንስት ወባ ኃይለ ዝንቱ አስማቲከ ኣሕድር  ወከዓው በላዕሌየ ሀበኒ ጸጋ ወኃይለ ወቅባዕ መልዕልተ ርእስየ ወኵለንታየ ቅብዐ መንፈስ ቅዱስ ጰራቅሊጦስ አስተሳልመኒ ወአስተፋቅረኒም ስለ ኵሎሙ ሰብአ ሃገር ከመ የሀቡኒ ሀብተ ወፈኑ ዘየዓቅቡኒ መላእክት ፍታሕ ማእሠረ እደዊሆሙ ወአራኅርኅ ልቦሙ ሊተ ለገብርከ…….መልአከ ሜሞሮስ ደቡባዊ ነፋስ ኃይለ ድብ ንጉስ ፩ ወእቱ መንፈስ ቅዱስ ሰንተው ቀንተው ቀርነው ቀርነለው አብያቴር ሰይፈ መለኮት ክቡድ ግርማ መለኮት ነድ ይርእድ ሞገሰ ዚአሁ ወጣዕመ ልሳኑ ወሣዕሣዐ አፉሁ ፍሡሕ በቀሓሹን ፫ ጊዜ። አቅመሐሹን ፫ ኵሎ አስማተ ዘይኳንን ሞገሰ መስቀሉ ምሉእ ወፍቅረ መንግሥቱ ጽኑዕ። ኢየሱስ ክርስቶስ ድማሄል ፫ አቅማሄል ፫ ብርሱ ባሄል ፫ ባኤል ፫ ዘትሁብ ዝንተ ኵሎ ሠናያተ ለውሉደ ሰብእ። በብዝኃ ጥበብከ በዝንቱ ስምከ ተማኅፀንኩ ወበዝንቱ ቃለ መለኮትከ ተወከልኩ ከመ ተሀበኒ ዮም ጥበበ መሥልጣነ ኃይለ ወመዊአ አኅድር በላዕሌየ ሀብተ ጸጋ ወኃይል ወክብር ወምላዕ ውስተ ገጽየ መንፈሰ ሰላም ወከዓው ሞገሰ ዘመላእክቲከ ሥዩማን ወበዝንቱ ቃለ መለኮትከ ፍታሕ ማእሠረ እደዊሆሙ ወእገሪሆሙ። ሚጥ ወአደንግፅ ልቡናሆሙ ወአራኅርኅ ሕሊና ሥጋሆሙ አስተፋቅረኒ ወአስተሳልመኒ ለእድ ወለአንስት ወምስለ ኵሎሙ ነገሥት ወመኳንንት ወሰብአ ወምስለ ኵሎሙ ነገሥት ወመኳንንት ወሰብአ ሀገር ከመ የሀቡኒ ንዋየ እስመ አንተ እንዚ እየ ወተስፋየ ወሞገስየ ለዓለመ ዓለም አሜን።

 

                          56

 

                   ውሂበ፣ንዋይ፣ውሢመት

 

     ጸሎተ /ውሂበ/ ንዋይ ወሢመት። አሸማከር አሸማኒአአሸማኒ ፍታሕ እደዊሆሙ ለነገሥት ወለመኳንንት ለጳጳሳት ወለኤጲስ ቆጶሳት ለቀሳውስት ወለዲያቆናት ለእድ ወለአንስት ለአእሩግ ወሕፃናት ወለኵሎሙ ውሉደ አዳም ወሔዋን ከመ የሀቡኒ ወርቀ ወብሩረ ልብስ ወሢመተ ሊተ ለገብረክ …..በስመ ራሙኤል አዩር ሊቅ ሐልቂቅ ምልቂቅ መሐሊሃን እምሩክ ግብተ ብሻ ልትተ ወያብተ ወአብተ ወያምአል ወያሩሩን ወያህኩን አፍኩን ወረሐምትት አማቲት ነረ ቀረ በኃይለ ዝንቱ አስማቲክ ፍታሕ እደዊሆሙ ለሰንአ ዝንቱ ዓለም ሰመ ያውጽኡ ንዋየእመዛግበቲሆሙ ወየሀቡኒ ንዋየ ወሢመተ ሊተ ለገብርከ ….ሰብሕዝማ ሐሙልያ ንደቅሎ ላህያ ሐጁር ነጁስ ሩስ መሊስ እንኩን ፍየሎ አኽያ ሸራ ኽያ በራኽያ አልሻዳይ ፀባዖት አዶናይ በኃይለ ዝንቱ አስማቲክ ሀበኒ ወትረ ተምኔትየ ወአድኅነኒ እምፀርየ ወጸላእትየ ሊተ ለገብርከ……

 

                          57

 

            በእንተ፣ውሂበ፣ ንዋይ፣ ወፍቅር።

 

     በስመ አብ በስመ ወልድ በስመ መንፈስ ቅዱስ በስመ ፩ አምላክ ወአስማቲሁ ለእግዚአብሔር በአስማተ ቅድስተ ቅድስት ሥላሴ ወነአምን ለሥላሴ በሥጋነ ወነፍስነ በስመ ሃሂ መልፈድፊድ ኃይለ መውደድ ላሾን አላሾን ፫ አለለዋሾን በስመ አብ አፋሾን ወበስመ  መንፈስ ቅዱስ አባሾን ደፀሹ በመጸጅ መጆርቲዎን አጀጅፋጪዎን አላቲዎን አላቂዎን አቅላዎን ስጡ አሰጡ ሚካኤል ወገብርኤል ሱራፌል ወኩሩቤል ዑራኤል ወሩፋኤል ሱርያል ወፋኑኤል አፍኒን ወራጉኤል ወሳቁኤል። ስጡ አሰጡ ፬ቱ እንሰሳ ጸዋርያን መንበሩ ለእግዚአብሄር ስጡ አሰጡ እምነገሥት ወእመኳንንት ስጡ አሰጡ እምነ ጳጳሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ስጡ አሰጡ እምነ ቀሳውስት ወዲያቆናት ስጡ አሰጡ እምነ እድ ወአንስት ስጡ አሰጡ እምነ አዕሩግ   ወሕፃናት ስጡ አሰጡ እምነ ወይዛዝር ወደንገጽር ስጡ አሰጡ እምነ ወታደር ወባላገር ስጡ አሰጡ እምነ ካህን ዘማሪ ወእምነ ጠቢብ ቆርቋሪ ስጡ አሰጡ እምነ ዓጣሪት ወቀባጣሪት ስጡ አሰጡ ለዘአኅዘ ወለዘኢአኅዘ ስጡ አሰጡ ድቅማኛዎችን ዱዱልሻዎን ሹሹልሻዎን አለታዎን አባቲዎን አጋቲዎን ስጡ አሰጡ ሶሮን ስብስትያኖስ ሰምየ ሶምያ ሰጡ አሰጡ ፍቅረ አዳም ወሔዋን ስጡ አሰጡ ፍቅረ ኖኅ ወሐይከል ስጡ አሰጡ ፍቅረ ብእሲ ወብእሲት ስጡ አሰጡ ፍቅረ መርዓዊ ወመርዓት ስጡ አስጡ ልበ ርኅሩኅ ወገጸ ፍሡሐ ኢላዋሒደተንከላሚሂም ቢል በልሸሪ አውሁወ ዓላኵሊሽይዒን ቀዲር ወዕልአላሁ ዐላሰይዲና አላሂ ወአለይሂ ወሷሒቢሂ ወሰላም ተዕሊመን ከሊሉን አዑድ ሜሮነ በርእስከ።

 

     የውሻ የዋሻ መሸና መሻቆጀ ያቀጁ ደቀጁ አብ እሳት ወልድ እሳት መንፈስ ቅዱስ እሳት የማነ ገሞራ እሳት በስመ ፫ አስማት ወበ፩ መለኮት አዑድ ሜሮነ ፫ ጊዜ። ስጡ አሰጡ ፍቅረ ንጉሥ ወንግሥት ፍቅረ ነፍስ ወሥጋ ስጡ አሰጡ ፍቅረ ፀሐይ ወወርኅ ስጡ አሰጡ ፍቅረ ሰማይ ወምድር ድግድጉ ኤል ፫ ድጉድብኤል ፫ ምስብኤል አምስብብኤል ፫ በከመ ሠወርኮሙ ለሄኖክ ወለኤልያስ እመላእክተ ሞት ጸዋጋን ከማሁ አርኅቅ እምኔየ ጽልአ ወጸብዐቂመ ወበቀለ ተስናነ ወባእሰ ዮም ወዘለዓለም ወእስከ ለዓለም ላዕለ ገብርከ……

 

     በመንፈቀ ሌሊት ዓዲ በነግህ በሜሮን ዓዲበቅብዐ ቅዱስ ዓዲ በዘይት ፯ ፯ ጊዜ ደግመህ ተቀባ። በስመ አብ በል ሸርዑል ጀማኤል በዝ አስማት አራኅርኅ ልቦሙ ለውሉደ አዳም ወሔዋን ከመ የሀቡኒ ንዋየ ወሢመተ ሊተ ለገብርከ……. ተሠጥቀ ኰኵሕ ወውኅዘ ደም የኔን ነገር ለእገሌ ሀቦ በሎ ገብርኤል ብለህ ፵ ጊዜ ደግመህ በማር ዋጥ።

 

                          58

 

                   በእንተ ፍቅረ ሰብእ።

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ጸሎት በእንተ ፍቅረ ሰብእ አስማቲሁ ወአስማተ ኃይላቲሁ ለእግዚአብሔር ዓቢይ ሃሃሃኤል አድናኤል ኤላኤል ላላላኤል አምላኤል ምላኤል ሓሓሓኤል ሐራዋኤል ማማማኤል ማሚመ ኑደኤል ሣሣሣኤል ራራራኤል ራሙኤል ኅደታኤል ቃቃቃኤል ቅላኤኤል ቀፍኤል ቀእታምኤል ባባባኤል ባቱኤል ታታታኤል ቱታኤል ኃኃኃኤል ኄርናኤል ኅብቋኤል ናናናኤል ናርናኤል ናቱኤል ናሙኤል  ኣኣኣኤል አኤል አክስብኤል ካካካኤል ካኤል ዋዋዋኤል ውናኤል ዘዘዘናፌል ያያያኤል ያሰራኤል ያናኤድ ደደደኤል ድማህል ጋጋጋኤል ጉጋኤል ጋቱኤል ጣጣኤል ጣኤል ጤንጓኤል ጳጳጳኤል አርጳኤል ጻጻጻኤል ጻቱኤል ፃፃፃኤል ፀበርትናኤል ፋፋፋኤል ፍትሥጋኤል ፈልፈላኤል ፍትሐናኤል ፓፓፓኤል ቈቍቍቋቋኤል ኰኵኵኳኳኤል ጐጕጕጓጕኤል ኈኍኍኋኋኤል ኋኋኋራቱኤል ካኤል አድናሌል በኃይለ እሉ ቃላት ኤድኤል ደሙራኤል ወበኃይለ እሉ አስማተ ኃይላት ክቡራት ተማኅፀንኩ ከመ ተሀበኒ ሞገሰ ወሥልጣነ ክብር ወገዕል ተፋቅሮተ ጸጋ ዘኢይማስን በኀበ ኵሉ በቅድሜከ እንዚኦ ወበቅድመ ኵሉ ሰብእ ወጸግወኒ ሀብተ ተፋቅሮ ሠናየ በቅድመ ኵሉ ፍጥረት ወኢታስተኃፍረኒ እምዘይትቃረነኒ ወሠውረኒ እመልእልተ ርእስየ እምዓይነ ኵሎሙ ሰብእ ጸላእትየ እኩያን ሊተ ለገብርከ…… ፩ ስሙ ለእግዚአብሔር አኽያ ሸራህያ በራኽያ ኤልሻዳይ ጸባኦት አዶናይ ዴንግአልፋ ወዖ አሌፍ ቤት ጋሜል ፩ ስሙ ለእግዚአብሄር እእተ ዋተራ አክራ ማለዮ ፓራ ፓእት አርጋግ ዳሌጥ ሄ ዋው። ፩ ስሙ ለእግዚአብሄር ማስያስ በትረያሬክ ዩድ ከፍ ላሜድ ፩ ስሙ ለእግዚአብሄር አስኪሊላ እስክ ጸላዝዮን ሰሎም ዔ ፌ ጻ ዴ ፩ ስሙ ለእግዚአብሔር ዐማኑኤል ዓሣ እእሶን ቃር ድአቡጣ ዓሣማኅሶን አፍርዮን ፍቅረ ጽዮን ታውለትቅረብ ሰዕለትየ ኅቤከ እግዚአ ኵናኤል ደናኤል አርጋኤክ ግሙናኤል ዮሴድ። ቃኤል በኃይለ ዝንቱ አስማተ ቃልከ መለኮታዊ ወበመስቀልከ ሰላማዊ ተማኅፀንኩ ሀበኒ ሞገሰ ክብረ ወብዕለ ወጸጋ ዘኢይት ወሰን በኵሉ መዋዕለ ሕይወትየ በቅድመ ኵሉ ሳብአ ዓለም ወጸግወኒ ሀብተ ተፋቅሮ ሠናይ ወኢታስተሐፍረኒ እምተስፋየ አርትዕ ወክሥት ነገረ ሀብትየ ሊተ ለገብርከ….ሎአደድ አሎደድ ኤልደደ ሜልዳድ ማር ወምድር ማር ማአብር አንተ፤ አንተ ውእቱ ቃለ እግዚአብሔር ኃያል ዘአስተፋቀርኮሙ ለሰማያት ወምድር ዮምኒ ከማሁ አስተፋቅረኒ ምስለ ንንት ወፈድፋደሰ ምስለ እገሌ አስተፋቅረኒ ሊተ ለገብርከ…. ገቢሩ ፍየለ ፈጅ ሎሚ ምስርች ወርካ ክትክታ እንቧጮ በለስ የጅብ ምርኩዝ ዋንዛ ቀጋ ተቀጽላቸውን በማይ ድገም ወበምራቅ 49 ጊዜ ድገም ቅባዕ ገጸከ እግዚኦ እግዚእነን ስምዐኒ አምላኪየ ስእለትየን ደምር ዓዲ ዕፍራን ፍየለ ፈጅ የጥንዡት የቁልቋል የዶቅማ ተቀጽላ ከ፫ የወይን ፍሬ ፩ ፩ ከውሥጡ አውጥቶ ፫ የሰሌን ፍሬ ደቁሶ በፍየል ስብ ለውሶ ቢሆን አዲስ ጐጆ ቢታጣ እንፁሕ ቤት ሣር ጐዝጉዞ የወይራ አልጋ ሠርቶ ፬ ባላ ላይ ወይራ ቅጠል ጐዝጉዞ በትናንሽ ፯ ሸህላ ያባይን ውሀ ሳይነጋገሩ ቀድቶ በፊተኛው ዕቃ ፹ ዕቃዎች ጨምሮ ካልጋው ላይ ሁኖ ፯ መብራት በዘንግ ቋጥሮ ይደግሟል። ፩ ፩ ጊዜ በ፬ ጊዜያት በነግህ በሠርክ በንዋም በመንፈቀ ሌሊት ከሸህላው አፍ በጥርስህ እየሸረፍህ ፍቅር ወሰላም ሊተ ለገብርከ እገሌ እያልህ ድገም። በቀይ ቀለም ጽፈህ ያዝ፤ ዓዲ በፍኖት ቅበር በላይ ኩስ።

                       

 

                          59

 

          ጸሎተ በእንተ መፍትሔ ሥራይ ወጥላ ወጊ።

 

      አራሁማ አራሂም ቆቆልያ አቢድንን መአነ ቢድን መመአአሲቡ ኑዱዳ ለኩም ድኩም ወላዱን ፍታሕ ወተፈታሕ ሥራያተ ኵሉ ነገር ዘተገብረ በላዕለ ገብርከ …… እምሸራ ለደ ሰደከ መሬረከለደፈከ ወዳዕሁከ መዘራከሰ አነ መአሲዮ ላረዮ ሰረፈ አዘረፈ ከንትብ ፈንከ ወአለውረቢክ ፈርህ ብቁሉ አአዙ ረቢ ልናሌ ኪናሌ ሂቅ አውዱን ፍታሕ እምላዕለ ገብርከ …….ወላሌ ክላሁ አላዠ ዝማአሟሆደ ለዱቡ አናዝባ ርፍሁ መመቲነ ነሐውሮ ወለነሐውሮ ቀተቶ  ለዘመጢጠ ሌሁ አላ ደሄም መረሰ ይቴን ፍታሕ የአዮሐል ከፈሩ አማታ እእጉዱ ወንቱም ፍታሕ  ሥራያተ ኵሉ ነገር ዘተገብረ በላዕለ ገብርከ .  .  . ገቢሩ ቁንዶ በርበሬ ሰሊጥ ያሞሌ ጨው ኮረሪማ ዝንጅብል ሎሚ ነጭ አዝሙድ ምስር  ጥቁር ስንዴ የአቱች ሥርና ቅጠል ሰልቀህ በሌሊት ውሀ በነጭ ዶሮ መረቅ ጠጣ ሥጋውንም ብላ ዓዲ በእስጢፋኖስ ማር ብላ ለእመ ገበርከ ለዝበርኅወተ ሰማይ እስከ ዕለተ ሞትከ የዓቅበከ እምጽላ ወጊ ወእመስተሐምም ወኵሎ ሥራያተ ሰብእ።

 

                          60

 

                    ነገረ ምሥጢራት

 

      ላህ ላህ ፯ ወላህ ፯ አላጁጅ አላጁድ ሰሩ ብሩ አርእዩኒ ነገር ኵሉ ፍጥረት ላህ ፯ ጰጰጲን ቃላት ድዮጰ ጸዓድዒድ ፈኑ ቃላቲከ ጁምጢና ጽዳኤል ጥፍነት ምቅዋዝሞ ማረ ወማረት ሰንሰን አሰንሰን ለዲሞ ለጢኖ ሏይ ይሏይ አሏያ ነገረ ሠናይ ወነገረ እኩይ በዕለተ እገ በወርኀ እገ ዘመነ እገሌ ላህአላሁማ መሔር ወረሸባ ከማኖስ ፯። በከመ ነገርከ ክሰክናኖስ ሊዶር ንግር ለሊባኖስ ከማሁ ንግረኒ ነገር ዚአየ ወነገረ እገሌ። ላህፈላ ኢላሂ ኢላላህ አስቦ ኢላጅ ኢላታም ኢነጸረከ ወጅን ሰውነከ ዲሞ ዲኖ ጉዳሌ ጥፍነት መቅዝዮን ማረ ወማረት ንዑ ፯ ከመክሙ . . . ጠሌንዥ ወፍ አንቁር የድግ ተቀጽላ ይኽን በራስህ አስረህ ፵፱ ፵፱ ጊዜ ዕጣን እያጤሱ  መድገም ነው ነጭ ዶሮ አርዶ ድጋሙ ሳይጀመር ክንፉን በመጠጫ ጠጣ።

 

 

                          61

 

                     ነገረ ራዕይ።

 

      ፋኢ ደኢ አዲድ ዳውድ ቡኒ ቄሲውት ፌዶ በርፌው አጋሞስ አርቃንዮ ጸናሊዎስ ምስሐበ ዛር አርእየኒ ነገር ኵነትየ ሊተ ለገብርከ….፯ ጊዜ ዲባ ርእስከ የምድር ዕንቧይ ስር ያዝ። ሹር ማር ፫ ጊዜ ግርማኤል ናትናኤል ክብርናኤል ዮም ነዓኀቤየ በሰላም ከመ ትንግረኒ ምሥጢረ ዝንቱ ዓለም ዘይከውን ወዘኢይከውን በዕፀ ሳቤቅ ፵፯ጊዜ ደግመህ በቀይ ሐር ጠምጥመህ በራስህ ላይ ይዘህ ደግመህ ተኛ።

 

 

                          62

 

               ጸሎት በእንተ ቅብዓተ ሞገስ

 

     ኔላላኤል ኪላላኤል ጲጲኤል አብላላኤል አውዚል አጅብን አጅብጅን ከራሆቤለ ጀልቤላ ማርሆላ በጽማኤል አኳኵኤል አዝቢቻቻኤል አራፎን ቃውላን ነዚላ አራኮን መጁር አራፎን መጰጱር ያያዊ ጨልጰኤል መቅኤርር ሸቅኤል ዘአድድ ሸፋድር  ኬል ቄድን በሸሐፍውካን ዘናቲር ማቲር ኬሮኖስ ርንማንድር ጌልጌሚድ ሐሐቸል አሸማድን በከለማቲን በከለሚቁን ሰምሮን ጨዋሸን ወያርኤል አሙዚል ሐሙድ ወሣህለ ገርዲን ሣህላ ጀውዘኤል ገዲናኤል ፓፓኤል ሐሮፓኤል በሐቅለ ወግኑን ለናህዲ ሱቡለና ሙአብያሺን። አስተፋቅረኒ ወአስተጻምረኒ ምስለ ነገሥት ወመኳንንት ወምስለ ኵሎሙ ደቂቀ አዳም ወሔዋን ለገብርክ…..በቅብዐ ቅዱስ ፺፱ ጊዜ የልደታ ዕለት ድገም ዓዲ ፯ ጊዜ ዕለት ዕለት እየደገምህ ገጽህን እንደ መስቀል እያማተብህ ተቀባ።

 

                          63

 

                   በእንተ እቃቤ ርዕስ።

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅድስ ፩ዱ አምላክ። ጸሎት በእንተ ዐቃቤ ርእስ ቄጅ መጅ መጅ ናን እረቀመጅ መከመጅ መማሽ ሹጁ አዑር አዕይንቲሆሙ ወአጽንዕ ልቡናሆሙ ከመ በድን ርኵስ ወከመ ዕብን ፍዙዝ ይኩኑ ነጌ ኩምቢያማ አውራሪስ ቀንዳማ ሰብእ ሰይፋማ ስልብ ልቦሙ ለሰብአ ኵሉ ዓለም ፀርየ ወጸላእትየ እገሌ ብለህ ፫ ጊዜ ድገም።

 

                          64

 

                   ጠላትን የሚያፈዝ

 

      መምትፊአል ፲፱ ፃፍ ኤውኮአል ለውርታ አህድ ፯ ጻፍ መላም ተአጀም ኤውሩ አላ የለውርታን አክድህ የእገሌን ልጅ እገሌን ነገሩን አፍዝዝ የኔንነገር አንግሥ ብለህ በጥቁር ቀለም ጻፍ በጥቁር አህያ ጋማ ነጭተህ በተጻፈው ወረቀት ጠቅልለህ ታጥነህ ሒድ ነገር እንዲቀር እንዲቀናህ።

 

                          65

 

                   ሹመት የማያሽር።

 

      ሐማያኤል ሐንያኤል ሐቅያኤል ሐስያኤል እንዘይብል ያማዕቆረ ረጡሐርያ ሩሐንያ አልኪራም አጠይቢን አላአሰማ ኢኩም አልሐናን ግበሩ በፍቅረዚአየ አግብአክሙ ኀበ እገሌ ሀቦ በሎ ገብርኤል የኔን የእገሌን ነገር ለእገሌ ገቢሩ ነጭ ዕጣንና ልባንጃ እያጤስህ በመንፈቀ ሌሊት ከመዳመጫ ደንጊያ ላይ ቁመህ ፵፱ ጊዜ ድገም። ሹመት የማያሽት የማያስከስስ ሕዝቡ የሚያፈዝ ደግሞ የመቃብር አፈር አምጥተህ በመንፈቀ ሌሊት ፵፱ ጊዜ ይስማዕከን ደግመህ ፫ ጊዜ ወደ ግራ አዙረህ በምትሠራበት ላይ በትን።

 

                ርኅወተ ሰናይ የሚውልበት።

 

      ጳጉሜ ፫ ቀን ጥቅምት ፩ ቀን ታኅሳስ ፲፪ ቀንየካቲት ፬ ቀን። መጋቢት ፳፯ ቀን። ግንቦት ፲፰ ቀን ሐምሌ ፲ ቀን ነው።

 

      የምዕራገ ጸሎት መነሻ መስከረም ዘመን ሲለወጥ ሰኞ ይጀምራል። ቁጥሩ በ፵፱ ቀን ይውላል ያመቱ ፯ ቀን ነው። ከእሑድ አይወጣም አይወርድም።ሰንበተ ሰንበታት በዓመት ፬ ቀን ነው። የሚውለው ማንሻው ዘጳጉሜ ፪ ቀን ነው። በ፺፩ ይገድፋል።

 

           መሥዋመ አጋንንት ወመርበብት ሰሎሞን።

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ጸሎት በእንተ መሥጥመ አጋንንት ወሰይጣናት ባርያ ወሌጌዎን ጀን ወደባስ ደስከ ወጉዳሌ ዛር ወትግሪዳ መጋኛ ወሾተላይ ንዳድ ወመንሾ ምትሐት ወጽፍዓት ጉስማት ወፍርቃቃት ውግአት  ወሰቅስቃት።  ኤልክሻካሽል ወተለካሽ ቡዳ ወቂመኛ አልጉምፌራ ወቸነፈር ፍልጸት ወቁርጸት ወቁርጥማት ዓይነ ባርያ ወዓይነ ወርቅ እደ ሰብእ ፍጌን ወሥራይ

 

     ዝ ውእቱ መጽሐፍ ዘወሀቦ ቅዱስ ሚካኤል ለሰሎሞን ንጉስ ከመ ያኅጕሎሙ ለአጋንንት እኩያን ሰማይ ወምድር መናብርቲሆሙ ለአጋንንት ወይቤ ሊቆሙ ዘስሙ ጋውል፤ ንነሥኦ ለሰብእ ወንነጽሖ ውስተ ሐመድ ወንመጽእ ኀቤሁ  በአምሳለ ጢስ ወጸበል ወንዘብጥ ናላሁ ናጠምም አፋሁ ወንከትር አዕይንቲሁ  ዓዲ ንበልዕ ሥጋሁ ወናጠፍእ ልቦናሁ ለእመ ኢሃሎ ዝንቱ መርበብት ንሕነ ንትፌሣሕ ብዙኀ። ወይቤ ፀርነ ዘስሙ ፊቂጦር፤ ሜራ ማሜራ ፒፓፒሎ ዐማኑኤል ፒፓሮስ ኢያኤል ሱቃኤል ኤልማስ ሱርሰማባሩ ሳሙኤል  ኤል አዴራ ምርምኡ እፍኤል ኢያኤል በኃይለ ዝንቱ አስማቲክ አድኅና እምአል ጉም መስተሐምም ወቁራኛ ለዓመትከ……..

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ጸሎት በእንተ መደንግጸ አጋንንት ወመሥጥሞሙ ለአጋንንት ጸዋጋን፤ ዘይትነበብ በዕለተ ሰኑይ ወዓቃቢ ሁኒ ቅዱስ ሚካኤል ውእቱ ወኮከቡኒ ቀመር። ኢላሂ ጃዛኩም አንሰሪፋ ኢለመወጢኪን አድስራኤል ረኹ ዚን ተሸተቱ ተሻተቱ አህላ ወሣህላ ወለሐውቆታ ወለሐወል ቦታ ሰዊቱን ሰውቱን ስርሕላ በቤኩም።በኃይላ ዝንቱ አስማት አድኅና እምሕማመ ባርያ ወሌ ጌዎን ፍጌን ዓይነ ሰብእ ወነሃቢ ለዓመትከ።

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ጸሎት በእንተ መሥጥመ አጋንንት ዘይትነብብ በዕለተ ሠሉስ። ወዓቃቢሁ  ቅዱስ ገብርኤል ወኮከቡኒ አልመኒሸ ሣምሮን በድኁድ ጌዢሮዢ ጌልማድን እማት ተልመት በሰቃ በጼቃ ለሽሜ መስሜን ዘነዘሎን በተለጥፍራትን ዘመግ ዜመግ ቱዝቱዝ ቱዝቱዝ ቀደከአአ ከፀኑአአ። በኃይለ ዝንቱ አስማት አድኅና እምሕማመ ማቋ ወግብጥ ወሌጌዎን ለአመትከ።

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ፀሎት በእንተ መሥጥመ አጋንንት ዘይትነበብ በዕለተ ረቡዕ። ወዐቃቢሁ ሱራፌል ወኮከቡኒ አማድር ጨተታ ኩኩታኤል ጨትኩታኤል ሸተኩታኤል ትትኩታኤል ጀትኤል ዝትኩኤል ኩታታኤል ሊ ሊ ሊ ሟ ሟ ሟ ሯ ሯ ሯ ሿ ሿ ሿ ፏ ፏ ፏ ሸ ሸ ሸ ኸ ኸ ኸ ጄ ጄ ጄ በኃይለ ዝንቱ አስማት አድኅና ለዓመትከ።

 

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ጸሎት በእንተ መስጥመ አጋንንት ዘይትነበብ በዕለተ ሐሙስ። ዓቃቢሁ ራጉኤል ወኮከቡኒ አልመሽ ተሪ። ሸኰዙሊ መጀሸፌዶ ሰልሁማ እኩቲ ዊዳራ ቁልሁና ጶናት አንቲል ቸምድምጉም አክርቲ ለኣርቱምፒ አፍርድ አርኪጥ፤ ሩምሲናሃ ቆሊሎ ሂሉዲቅን አቁዲ፤ አሰረ ሰለኪስ ቃሉ ወሕሊና፤ ቃሊኛ፤ በኩሽ አክልቴ ወቀዱታት ቹተጀ ጀጂማ ጀደጁ ሐፀሬ ሸዋርዳን በሸዋርዳን ሸውር በዘጋዜንተ ንጉሥ በኢዮብ ንጉሥ ኣጋሮም ክሸርሞ ፈታሒ ደሰል ሲኖዳ ቃሮድ በጁሐም ፍዘታ በጁሐም ፍዘዙ ቅዘዙ ጨትኩታኤል። ዘአብረርኮሙ ለአእዋፈ ሰማይ ሰማየ ቀፊጸከ ወባሕረ በጽቢጸከ ከማሁ ስድዶሙ ወአስጥሞሙ ለአጋንንት ርኵሳት ባርያ ወሌጌዎን ዛር ወደባስ ወትግሪዳ በስሙ ለኢየሱስ ክርስቶስ አድኅና ለዓመትከ።

 

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ጸሎት በእንተ መሥጥመ አጋንንት ዘይትነበብ በዕለተ ዓርብ። ዓቃቢሁ አፍኒን ወኮከቡኒ ኣልሸራ። አራኮን ከናንኅ አናንኅ አምኖይኅ ንጋርተን ንትገርተን ንትንንትሃ ኅብስተ ፈለሀፏመሸሊ ፒሕ ጨለጶ ፀለፐ ተልብያኛ ኢትከነኛ ከሸፒ ኢተከሸከሸ ኪካምሽ ኢካምሽ ኢትናክ ኢትናካን ኢተጰሥጋን ኤንጰጲ ጰንኞሮን በርቤዳን ብርን ፀልሒም። በኃይለ ዝንቱ አስማት አድኅና እምሕማመ ቡዳ ወከልከሌዎስ ዛር ወድድቅ ወጉዳሌ ለዓመትከ።

 

      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ጸሎት በእንተ መሥጥመ አጋንንት ጸዋጋን፤ ዘይትነበብ በዕለተ ቀዳሚት። ዓቃቢሁ ዑራኤል ወኮከቡኒ ዛሕል፤ አሲደዶና ከልዳኒ ሃሊሸውጠሬ ሸሸሬ ታሆሚና ሰለረጅ ሽሩ ጨማ ሐረነ ልጫም ጨፍሊት ወጨደ በዲር ዲራቱስ ዘተክታብ በራሑ ፀላም እድ እስማዕ በቀርሞን በጀርሞን በቃስርሞን እልመክኑን ረቢና ሸርሞን አኽያ ሸራኽያ ኤልሻዳይ ፀባዖት እልመክኑን ዐማኑኤል ጌክ በጼቃ ቀርነ ሓሹል ዘነበረ ውስተ ቤተ ሰሎሞን። በዝንቱ አስማቲከ ዕቀባ እምደዌ ሥጋ ወመጋኛ ለዓመትከ።

 

      ጸሎት በእንተ መፍትሔ ሥራይ ዘይትነበብ በዕለተ እሑድ። ኪን ወእደ ሰብእ ጠቢብ ወነሐቢ ብእሲ አው ብእሲት ሐበረደጁን ምርታዶ ምርታዶ አክሎግ አክሎክ ኤፍዛዜዎን ኤፍዛዜዎን ሐረጅ ሐረጅ ዶር አላዶር ሔጅረጅ ሔጅረጅ በስመ ሐበረዶን አንተ ውእቱ ሥራይ ተፈታሕ ሥራየ ፍቍራን ወደብተራ ሥራየ ብእሲ ወብእሲት ሥራየ አረሚ ወክርስቲያን ዘተገብረ በመብልዕ ወበመስቴ ወዘይገብሩ ሥራያተ እኩያን መሠርያን ሰማየ ነጺሮሙ ወምድረ ጐድጕዶሙ ታቦተ ገሢሶሙ ወዕጣነ ወጊሮሙ ስብሐ አጢሶሙ ወአንቆቅሖ ደጊሞሙ ሰርዶ ወአሥዋር መሊሖሙ ወከርካዐ መቲሮሙ ዘንተ ኵሎ ዘይገብሩ ፍታሕ ሥራያቲሆሙ ወሰዓር ድጋማቲሆሙ ከመ ኢይቅረቡ ኀበ መንገለ ሥጋሃ ወነፍሳ ለዓመትከ……… ለዓለመ ዓለም አሜን።

 

 

         ከመጽሓፈ ፅፀ ደብዳቤ የተገኙ መድኃኒቶች።

 

      ፩፤ ለትልቁ የደዌ በሽታ፤ መጀመሪያ የቁልቋል አበባ በማር ለውሶ መቅባት ፪ኛ፤ ያባሎ ፍሬ ከእነቅጥሉ በአንድነት ወቅጦ መደምደም ነው። የሰባውንም የዘንዶ ሥጋ ማብላት ነው። ወይም የጥንቸል ራስ ቀቅሎ በውስጡ መንከር ነው።

 

     ፪፤ እግሩ ለአበጠ ሰው(ከማን አንሼ)፤ የዘንዶ ሞራ  ወይም የዝንጀሮ ሙርጥ የአጋዘን ስብና የሰጎን ዕንቍላል ማሠር ነው።

 

     ፫፤ሽንቱን ለከለከለው ሰው፤ ዝባድ በቡና ጨምሮ ማጠጣት ወይም ከሙቅ ውኃ ላይ ማስቀመጥ ነው። ወይም እንስላልና የቲማቲም ቅጠል አብስሎ ውኃውን ማጠጣት ነው።

 

      ፬፤ ጆሮው የደነቁረ ሰው፤ የሰሊጥ ቅባኑግ ቅባኑግ ቅዱስ የፍየል ቅቤ የአቱች ቅጠል ደቁሶ ይህ ሁሉ ውኃውን አዋሕዶ በቀትር ፀሓይ አስተኝቶ በጆሮው መጨመር ነው።

 

     ፭፤ የጨብጥ መድኃኒት፤ ዋዢብጥ ክንፏን እግርዋን ራሷን ቈርጦ ጥሎ የቀረው አከላቷና የምድር እምቧይ የአሰርኩሽ ተበተብኩሽ ሥር ፩ ላይ አልሞ ሰልቆ በማር መዋጥ ነው። ጥላ ተከልከል የገብስ ጠላ ጠጣ ሲያደክመው ወተትና የዶሮ ጉበት መስጠት ነው። ፪ኛ የበልድ በልዶ ቅጠል አልሞ ደቍሶ በወተት በጥብጦ ማጠጣት ነው።

 

     ፮፤ ፅንስ አጥንት ለሆነባት ሴት፤ የኮክ ቶቀጽላ ባሏ ቈርጦ ደቍሶ በውኃ አጠጥቶ ዕለቱን በሩካቤ ቢገናኛት ሰው ሁኖ ይወለዳል።

 

     ፯፤ ለኪንታሮት፤ የዕፀ ሳቤቅ አረግና የሞዴር አረግ የሮቢያው ዕንጨት ከ፫ቱ በተገኘው በአንዱ አጥብቆ ቢተኰስ ቅጽበት ይድናል።

 

     ፰፤ ለእብጠት፤ አብሽ ባቄላ የፍየል በጠጥ አልሞ ፈጭቶ እንደ ተልባ መትቶ ማሰር ነው። ጥሬ ተልባም አገንፍቶ ማድረግ ጥሩ ነው።   

 

     ፱፤ ለመካን ሴት፤ የፈረስ ወተት የበቅሎ ኰቲና የዝኆን ጥርስ ፍቀት በርግመቷ ጨምረው ቢአጠጧት ትወልዳለች።

 

     ፲፤ እስኪቱ (ብልቱ) ለሞተበት ሰው፤ የዕሬት ሥር በቅቤ ለውሰህ ቅባው እግዚአብሔር ቆመን ፮ ጊዜ ደግመህ በጕማሬ አለንጋ ፍቀህ ዕጠነው።

 

    ፲፩፤ ለውርዴ እርጉዝ ሕፃኑን እንዳይጋባው ፯ ወር ሲሆነው የፍሕሦ ሥር አድርቆ አልሞ ደቍሶ በማር ፫ ጥዋት መዋጥ ነው።

 

    ፲፪፤ የእንግዴ ልጅ እምቢ ሲል፤ የምድር እምቧይ ሥር አውርዶ እያሉ ላዩን ፯ ጊዜ ቈርጦ ጥሎ ሥሩን   ነቅሎ ቀጥቅጦ ማጠጣት ነው።

 

    ፲፫፤ ለቈላ ቁስል፤ የጐርጠብ ቅጠል አልሞ አጥቦ መነስነስ ነው። ነጭ ሽንኩርትና ሚጥሚጣም መልካም ነው።

 

    ፲፬፤ ለቺፌ፤ የደጋ አባሎ ፍሬ የምድር እምቧይ ሥር አልሞ በማር ወይም በቅቤ ማድረግ ነው።

 

    ፲፭፤ ለብልዝ ቁስል፤ የዓጋዘን ወይም የአሳማ ሞራ ማሠር ነው።

 

    ፲፮፤ ለመካን ሴት፤ የጥንቸል ጡት ቈርጠው ቢያበሏት ትወልዳለች።

 

    ፲፰፤ የአሳማ ዓጥንት አልመው ደቍሰው ቢጠጡት ማናቸውም በሽታ አይጋባም።

 

    ፲፱፤ ዓይንና ጥፍር ሽንትም ብጫ ለሚያደርግ በሽታ በትግርኛ (ዒፍሽዋ ወይባ) በጥልያንኛ (Febre Gialla) በአማርኛ (? ……) መድኃኒቱ፤ የብሳናና የስምዕዛ ፯ ፯ የጫፉን ቅጠል አብስሎ ደቁሶ በቅቤና አዋዜ ተሠርቶ በትንሽ እንጀራ ለክቶ ፫ ጥዋት መብላት ነው። አጓትም አብዝቶ መጠጣት ያስፈልጋል።

 

     ፳፤ የሳል (ሳምባ በሽታ ቱበርክሎዝ) የዕፀ ራምኖን ሥርና የበለስ ተቀጽላ ሥር ማርና ወተት አፍልቶ ጠጥቶ አድሮ ጥዋቱን በጥንባሆ መጠጫ ፯ ቀን መጠጣት ነው። ወይም የትልቁ የነጩን የእምቧይ ፍሬ አጥቦ አድርቆ አልሞ ደቁሶ እንደ ሻይ እያፈሉ ከቅቤ ጋር አዘውትሮ መጠጣት ነው።

 

     ፳፩፤ ደም ለሚያስቀምጠው፤ ፌጦ በእርጎ መትቶ ማጠጣት ነው። ወይም ትኩስ ብርንዶ ሥጋ መብላት።

 

     ፳፪፤ ለዓይን፤ ከ፯ የጠምበለል ወይም የወይራ ቅጠል ለንቃውን አልሞ ደቁሶ በነጭ እራፊ ውኃውን ማንጠብጠብ ነው።

 

     ፳፫፤  ለቂጥኝ፤ ዘርጭ አቢዶ የእምቧይና የችፍርግ ሥር በ፩ነት ሰልቆ በማር መዋጥ ነው።

 

     ፳፬፤ ለቁርጠት፤ ምስርች የብሳና ቀምበጡን የእምቧይ ሥርን ፩ነት ደቁሶ በለስታ ቅቤ ማዋጥ ኋላ ወገሚት ማጠጣት ነው።

 

     ፳፭፤ ለወስፋት፤ የቍልቋል ደም ፯ ጠብታ በትኩስ እንጀራ ላይ አድርጎ ጦም አድሮ ጥዋት መዋጥ ነው። መሻሪያውም የዶሮ ጭንጭራና አጓት ነው።

 

     ፳፮፤ ኮሶ፤ ለሚያዳግመው ሰው ጦም አድሮ ኮሶውን በወተት በጥብጦ ማጠጣት ነው።

 

     ፳፰፤ ለጐርምጥ ቁስል ተልባና ማር ለውሶ ማሠር ነው።

 

     ፳፱፤ ለቺፌ፤ ብዙ ጊዜ ከመቃብር የቈየ የሰው አጥንት አሳርሮ ቆልቶ በቅቤ ለውሶ ማሠር ነው።

 

      ፴፤ ሰውነቱ እየመነመነ ብዙ ቀን ለእሚታመም ሕፃን፤ የአሽኮኮ ሥጋ ማብላትና መረቅዋንም ማጠጣት ነው።

 

     ፴፩፤ ደረቅ የሆድ ቁርጠት ለእሚነሣበት፤ የእቧይና የአብላሊት ሥር ወይም የጥንጁትና የጠምበለል የእምቧይ ቅጠል ላንቃውን ከተገኘው ሁሉ ፩ዱን አኝኮ መዋጥ ነው።

 

     ፴፪፤ ጀማቱ የታሠረ፤ አብሽና ማር አጕርፎ አዘውትሮ እየተመገበ በእሚአመው ቦታ ላይ የዝንጀሮ ቂጥ ወይም የሰጐን ዕንቍላልልና ስብ ማሠር ነው።

 

    ፴፫፤ (ጀርባው) ለእሚገለበጥበት፤ የዋጊኖስ (መሊጣ) ፯ ፍሬ በወተት አብስሎ ፫ ጥዋት ማጠጣትና መሻርያውም የዶሮ መረቅ ነው።

 

    ፴፬፤ ሆዱን ለእሚነፋውና ደቃቅ ትል (ፍገ)ለእሚወጣው የዓሣ ቋንጣ አብስሎ መረቁን መጠጣት ነው።

 

    ፴፭፤ ለሻህኝ፤ (ግዛዋ) በልድ በልዶ (በትግርና ሕንድቝድቝ) ደሙን ፫ ጊዜ መቀባት ነው።

 

    ፴፮፤ ዓይኑ ታሞ ብርቱ ሥቃይ ለያዘው ሰው፤ የአህያ ጆሮ ደም ትኩሱን ፩ ጠብታ ማግባት ነው።

 

    ፴፯፤ በእጅና በእግር ለእሚወጣ ኪንታሮት በፌጦ አገዳ መተኰስ ወይም አሲድ ማድረግ ነው።

 

    ፴፰፤ለሻህኝ፤ ጨውና ነጭ ሽንኩርት ደቁሶ በስንዴ ሊጥ ላይ የቍልቋል ደም ጨምሮ መለጠፍ ነው።

 

     ፴፱፤መገረም ለተባለው በሽታ፤ በትግርኛ ዕንቅ ፍትሓ ወይም መምስሕ መንደፍያ ልት የተባለውንና የእንቧይ (ዕንጕለ) ቅጠሉን ደቍሶ በማር ለውሶ መዋጥና በአበጠውም ላይ ማድረግ ነው። ፀሓይና እሳት ጠላም ክልክል ነው።

 

    ፵፤ በዓይነ ቆዳ ውስጥ እከክ መስሎ ለእሚወጣው በሽታ (ትራኮማ) ቆዳውን ገልብጦ በነጭ ሸቢ መተኰስ (ማከክ) ነው።

 

    ፵፩፤ የእባብ መድኃኒት በአማርኛ የአህያ ጆሮ የሚባለው ሥሩ ፫ ፬ የእንሶስላ አምሳያ ነው መራራነቱም ከዕሬት ይብሳል። አስቀድመው በልተውት ቢነክሱ ከቶ አያስጐዳም ፍቱን ነው።

 

   ፵፪፤ ለጉንዳን፤ዊትያስ ትያስ አዛርያስ አውጽእ ጉንዳነ እምቤተ ገብርከ …….፮ ፯ ጊዜ ደግመህ በማይ እርጭ።

 

   ፵፫፤ የጥቁር ዶሮ ብልት አድርቆ ቢይዙት ግርማ ሞገስ ይሆናል።

 

   ፵፬፤ ለጉንዳን፤ ዊትያስ ትያስ አዛርያስ አውጽእ ጉንዳነ እምቤተ ገብርከ…… ፮ ፯ ጊዜ ደግመህ በማይ እርጭ።

 

   ፵፭፤ መካን ሴት፤ የጥንቸል ጭንቅላት በክታብ ይዛ ከወንድ ጋር ብትገናኝ ትወልዳለች።

 

   ፵፮፤ለሰላቢ፤ የጅብ አርና እንጀራ በጨው ጨብጠህ በዕቃው እሠር።

 

   ፵፯፤ ለቁርጥማት፤ የአብላሊትና የጠለንጅ የጠንበልና የኮሽሽላ ሥራቸውን ልጃገረድ በፈተለችው በግራ ፈትል ጠምጥመህ ከትበህ ያዝ።

 

   ፵፰፤ በመኝታው ለሚሸና የሰው አጥንት የእንስስትና የዓሣ ራስ በግራ ፈትል አስይዝ።

 

   ፵፱፤ ከብትን አራዊት እንዳይበላው፤ ዘየሐድር በረድኤተ ልዑልን ፫ ጊዜ ድገም። ቲት ራታስ አሽዮስ ምንኤል ዐማኑኤል ፈልልቆልል በስመ አርቄምስ አርቄና ዘውእቱ ማእሠሪሆሙ ለአራዊተ ገዳም ከመኢይብልዑ ሰብአየ ወእንስሳየ ሊተ ለገብርከ…….

 

    ፶፤ ቡዳ ለበላው መድኃኒቱ ቀጠጥና አጋም ግመሮና ስሚዛ (ሰንሰል) የቁራ አረግና የምድር እንቧይ፤ልምጭ ሥራቸውን በወይራ አንካሴ ያልባለገ ንጹሕ ልጅ ራቁቱን ምሶ በቀንድ ቢላዋ ቈርቶ በአልቲትና በድመት ጠጉር በጤና አዳም ፍሬና በነጭ ሽንኵርት አጣፍቶ ባፍንጫውና ባንገቱ ግበር የሚቆፈረውም በጳጉሜ ነው።

 

   ፶፩፤ ለነቀርሳና ጆሮው ለሚመግል፤ ለበለስ ቅጠል ጨምቆ ውኃውን ቢጨምሩበት ይድናል በጣም አታብዛ ያመግለዋል። የቅል ቅጠል ብቻ አሽተው ቢጨምሩበትም ይድናል።

 

   ፶፪፤ ጡትው ላበጠ እመጫት ጅማቱም ለተሸመቀቀ ዓዲ ለጆሮ፤ የሮማን ቅጠል አሳርሮ ቢያስሩት ይበጃል ከዝንጅብል ጋር ቅባ።

 

   ፶፫፤ በዱላም ሆነ በሌላ ነገር፤ ራሱ ለደቀቀ የደደሆ የንተም የብርብራ ቅርፊታቸውን ሰልቀህ በራሱ ላይ እሠር።

 

   ፶፬፤ እኽል እንዲበረክት፤ የብሳና ሥር የአጋም ሥር የገማ ዕንቁላል የከረመ ጭድ ዕጣን በጉሎ ቅጠል ሸፍኖ አውድማውን፤ ፫ ጊዜ በቀኝ አዙሮ ደንጊያ መጫን ነው፤ እኽሎ ከገባ በኋላም በጐታው ውስጥ አስቀምጥ።

 

   ፶፭፤ ለቁርጥማት፤ ለሰውም ለከብትም ቢሆን ቱልትና የዘርጭ እንቧይ ሥራቸውን አንድ ሲኒ አጠጣ።

 

   ፶፮፤ አብሶ (ዕፀ ፋርስ አስተናግር) በበርኻ የበቀለ ነጩ  ፍሬውን ደቍሶ በነጭ ሽንኵርት ብቻ በተደለዘ በርበሬ ሽሮ በነጭ ጤፍ እንጀራ እየፈተፈቱ መልክአ ኢየሱስን እየደገሙ ፯ ቀን ለክተው ለሕፃናት ቢያበሏቸው ትምህርት ከመ ቅጽበት ይገባቸዋል ፍቱን ነው። እንዲሁም ከመ ዘኢያገድፍም ፫ ቀን ጠዋት ጠዋት ማዋጥ ነው።

 

                  ————————

 

 

 

                          69

           

                ሐሳበ ጽንዕት ወጽንጽንት።

 

      ዕንጨት ተቆርጦ የሚነቅዝበትና የማይነቅዝበት የ፲፪ ወርና የቀን ቍጥር እንደሚከተለው ነው።

 

      ፩ኛ ከመስከረም ፩ ቀን እስከ ፲፭ ጽንዕት ከ፲፭ እስከ ፴ ጽንዕት ከ፲፭ እስከ ፴ ጽንጽን።

 

      ፪ኛ ከጥቅምት ፩ ” – ፳፫ ” ከ፳፫ – ፴ “

      ፫ኛ ከኅዳር   ፩ ” – ፱   ” ከ  ፱ – ፴ “

      ፬ኛ ከታኅሣሥ ፩ ” – ፳፫ ” ከ፳፫ – ፴ “

      ፭ኛ ከጥር     ፩ ” – ፲፯ ” ከ፲፯ – ፴ “

      ፮ኛ ከየካቲት ፩ ” – ፭   ” ከ  ፭ – ፴ “

      ፯ኛ ከመጋቢት ፩ ” – ፰   ” ከ  ፰ – ፴ “

      ፰ኛ ከሚያዝያ ፩ ” – ፲፩ ” ከ፲፩ – ፴ “

      ፱ኛ ከግንቦት ፩ ” –                 ፴ “

        ፲ኛ ከሰኔ     ፩ ” – ፳፬ ” ከ፳፬ – ፴ “

      ፲፩ኛ ከሐምሌ   ፩ ” – ፲፮ ” ከ፲፮ – ፴ “

      ፲፪ኛ ከነሐሴ   ፩ ” – ፳፫ ” ከ፳፫ – ፴ “

 

የሰውን ማርጀትና አለማርጀትም በዚሁ ሐሳብ ያስኬዱታልና እውነት ይሁን ሐሰት ግን ልኩ አይታወቅም።

 

      ፲፪ቱ ከዋክብት ደግሞ ፫ቱን በ፩ ወገን እየሆኑ በ፬ ባሕርይ፤ መሬት ማይ ነፋስ እሳት ተብለው ይመደባሉ።

 

ሠውር ጀዲ ሰንቡላ በመሬት ይመሰላሉ።

ሸርጣን ዓቅራብ ሑት በነፋስ    “

ሐመል አሱድ ቀውስ በእሳት      “

 

      ፲፪ ከዋክብት በ፲፪ ወር ውስጥ ተራ ይሾማሉ።

 

፩ኛ   ሐመል       መጋቢት    ምሳሌው አውራ በግ

፪ኛ   ሠውር        ሚያዝያ        ”     በሬ (ሶር)

፫ኛ   ገውዝ  ግንቦት        ”     ጥንድ

፬ኛ   ሸርጣን  ሰኔ           ”  ጐርምጥ

፭ኛ   አሰድ  ሐምሌ              ”  አንበሳ

፮ኛ   ሰንቡላ ነሐሴ          ”  ሽቱ (ሽቷም)

፯ኛ   ሚዛን  መስከረም      ”     ሚዛን

፰ኛ   ዓቅራብ  ጥቅምት    ”  ጊንጥ

፱ኛ   ቀውስ  ኅዳር          ”     ቀስተኛ

፲ኛ   ጀዲ   ታኅሣሥ             ”     የፍየል ጥቦት

፲፩ኛ ደለዊ   ጥር           ”     መቅጃ ማሕየብ

፲፪ኛ ሑት    የካቲት        ”     ዓሣ           

 

                  ———————

 

                          70

 

                  መጽሔት በዓታት ዘእሑድ

 

      ፩ ሰዓት ፀሓይ ነው ለፍቅር ለቤት ለቤተ ንጉሥ አዲስ ለመልበስ። ፪ ሰአት ዝኁራ ነው፤ ኢትግበር ምንተ። ፫ ሰዓት አጣርድ ለፍቅር ወለጽሐፈት ለኩሉ ሠናይ። ፬ ሰዓት ጨረቃ አትሽጥ አትለውጥ።፭ ሰዓት ሰው ከሰው  ለማጣላት ግበር። ፮ ሰዓት መሸተረ ለኵሉ ሠናይ። ፯ ሰዓት ምንም አታድርግ ኢይከውን።፰ ሰዓት ፀሓይ ወደ ነገሥት ለመግባት ለበጎ ነገር ሁሉ ሠናይ። ፱ ሰዓት ዠኁራ የሰው ልብ ለማራራት ሠናይ ። ፲ ሰዓት አጣርድ ለበጎ ነገር ሁሉ ሠናይ ፲፩ ሰዓት ጨረቃ  ለጠልሰም ሠናይ ፲፪ ሰዓት ዙኃል ለኵሉ ነገር እኩይ።

 

 

                                 ዘ ሰ ኑ ይ ።

 

      ፩ ሰዓት ጨረቃ ጠላት ለማሰር ሠናይ። ፪ ሰዓት ዙኃል ለመንገድ ለተግባር ሁሉ ሠናይ ፫ ሰዓት መሽተሪ ክታብ ለመፃፍ ለግቢ ሠናይ ኮከብ ፬ ሰዓት መሪካ ጠላትን ለመራገም። ፭ ሰዓት ፀሓይ ለተግባር ሁሉ ደግ ነው። ፮ ሰዓት አልማዝኁራ ለጠልሰም ለበጎ ነገር ሁሉ ሠናይ ፯ ሰዓት አጣርድ የሰው ልብ ለመሳብ። ፰ ሰዓት ጨረቃ ለመጋባትና ሰው ለማስታረቅ ሠናይ። ፱ ሰዓት ዙኃል ሰውን ከሰው ለማጣላት። ፲ ሰአት መሽተሪ ለበጎ ነገር ሠናይ። ፲፩ ሰዓት መሪክ ደም ለማፍሰስ ሠናይ። ፲፪ ሰዓት ፀሐይ የሰው ልብ ለማራራት።

 

                                  ዘ ሠ ሉ ስ።

 

      ፩ ሰዓት መሪክ ለመራገም ነው። ፪ ሰዓት ፀሓይ ምንም ነገር አታድርግ እኩይ። ፫ ሰዓት ዝኁራ ሴት ለማጨት ለማግባት ሠናይ። ፬ ሰዓት አጣርድ ለመሸጥ ለመለወጥ ሠናይ። ፭ ሰዓት ጨረቃ ለኩሉ ነገር እኩይ። ፮ ሰዓት ዙኃል ለዓይን መድኃኒት ለማደረግ ውል ለመያዝ። ፯ ሰዓት መሽተሪ ሁሉን አድርግ። ፰ ሰዓት መሪክ ለደም መድኃኒት ግበር።፱ ሰዓት ፀሓይ የሰው ልሳን ለማሰር ለፍቅር ለማግባት። ፲ ሰዓት ዝኁራ ምንም አታድርግ። ፲፩ ሰዓት አጣርድ ሴት ወደ ባሏ አትሂድ ፲፪ ሰዓት ጨረቃ ሰው ለማጣላት ሴት ለማፋታት።

 

                                   ዘ ረ ቡ ዕ።

      ፩ ሰዓት አጣርድ  ሰው ለማቃረብ ለኵሉ ነገር ሠናይ። ፪ ሰዓት ጨረቃ ምንም አታድርግ አኮ ሠናይ። ፫ ሰዓት ዙኃል ሰው ለማስታረቅ ደም ለማፍሰስ። ፬ ሰዓት መሽተሪ የወደድኸውን ሁሉ አድርግ።፭ ሰዓት መሪክ ሰው ለማጣላት ነው። ፮ ሰዓት ፀሓይ በባሕር በየብስ ለመሄድ ለኵሉ ሠናይ ።፯ ዝኁራ የወደድኸውን ሁሉ አድርግ። ፰ ሰዓት አጣርድ ባለጋራ ለማስታገስ ለነገርም ሠናይ። ፱ ሰዓት ጨረቃ ሰው ለማስታመም አድርግ ፲ ሰዓት ዙኃል ሴት ለማግባት ቤተ መንግሥት ለመሄድ ፲፩ ሰዓት መሽተሪ ውል ለመያዝ ከዳኛ ለመገናኘት። ፲፪ ሰዓት መሪክ የሰው ነገር ለማስነሣት ለጥል።

 

 

                           ዘ ሐ ሙ ስ።

 

      ፩ ሰዓት መሽተሪ ከብት ለመሸጥ ለመቀባበል። ፪ ሰዓት መሪክ መንገድ አትሂድ ቢሆን ውል ያዝ።፫ ሰዓት ፀሓይ ኢትሑር ርሑቀ ፍኖተ። ፬ ሰዓት  አልዥኁራ ለፍቅር ለመጋባት ሠናይ። ፭ ሰዓት አጣርድ ከወንድም ከሴትም ለመዋዋል። ፮ ሰዓት ቀመር መንገድ ለመሄድ ሠናይ። ፯ ሰዓት ዙኃል ከዳኛ ለመገናኘት ለነገርም ሠናይ። ፰ ሰዓት መሽተሪ ለበጎ ነገር ሁሉ ሠናይ። ፱ ሰዓት መሪክ ከነገሥታትና ከመኳንንት ቤት ግባ ፲ ሰዓት  ከማሁ ውእቱ ኮከቡኒ ፲፩ ሰዓት ዙኃል ለፍቅር ሠናይ። ፲፪ ሰዓት አጣርድ አልቦ ሠናይ ወእኩይ።

 

                           ዘ ዓ ር ብ ።

 

      ፩ ሰዓት ዝኁር ለፍቅር ሴት ለማጨት ሠናይ። ፪ ሰዓት አጣርድ ለጠልሰም ለኵሉ ሠናይ። ፫ ሰዓት ጨረቃ ለኵሉ  ነገር እኩይ። ፬ ሰዓት ዙኃል ለምንጭ ለሁሉ ጉዳይ መልካም። ፭ ሰዓት መሽተሪ ከሴት ለመገናኘት ለጽሕፈት። ፮ ሰዓት ፀሓይ ቤተ መንግሥት ለመግባት ሠናይ ፯ ሰዓት ዝኁር ሾምሾ ሴት ለግቢ ለማጨት። ፰ ሰዓት አጣርድ ዝኁራ ሁሉ ይፈጸምልሃል። ፱ ሰዓት አጣርድ ሰው ለማጣላት ሠናይ ፲ ሰዓት ጨረቃ ዙኃል ኮከቡኒ። ፲፩ ሰዓት ዙኃል መሸተሪ ኮከቡኒ። ፲፪ ሰዓት መሪክ በኒህ በ፫ቱ ለተግባር ሁሉ ሠናይ።

 

                                ዘ ቀ ዳ ሚ ት።

 

      ፩ ሰዓት ዝኁራ ለፍቅር ሁሉ ሠናይ ደግና ቅዳሜ ቀን መባቻ ሆኖ ቢገኝ ለሁሉ መልካም ነው ከዕለታቱ ሁሉ የመጀመሪያው ወር ዙኃል ሲገኝ እጅግ መልካም ይሆናል ፪ ሰዓት መሽተሪ ለዕርቀ ሠናይ። ፫ ሰዓት መሪክ ሰው ለማጣላት ግበር ሆሣዕና። ፬ ሰዓት ፀሓይ ከነገሥት ለመገናኘት። ፭ ሰዓት ዝኁራ ለዓይን መድኃኒት ግበር ሠናይ። ፮ ሰዓት አጣርድ ከማሁ ግበር። ፯ ሰዓት ጨረቃ እኩይ በኵሉ ፰ ሰዓት ዙኃል ለደም ጻፍለት። ፱ ሰዓት መሽተሪ ሠናይ ለኵሉ። ፲ ሰዓት መሪክ ለክፉ ሁሉ ነገር ግበር ይሰምር ፲፩ ሰዓት ፀሓይ ዝኁራ ለፍቅር ለዕርቅ ሠናይ ፲፪ ሰዓት ለነገሥት ለሁሉ መልካም።

 

 

                          71

 

                   ሐ ሳ በ ዳ ዊ ት ።

 

      ስምና ያባት ስም ዓመት ዓለምና ዓመተ ምሕረት። ዕለተ ዓርብና ስመ አዳም። ስመ ዳዊትና ወንጌላዊ በ፻፶ ግደፍ። ከዳዊቱም ከመጀመሪያው እስከ ፭ኛው መስመር ተመልከት።

 

 

 

                          72

 

               እንሰራ በመቃ ላይ ለማቆም።

 

      እንስራውን ውሀ ሞልተህ በመቃ ላይ አቁመህ ሺ በሺ ዕቃ ይቁም ዕቃ ወበመቃ አርዲ ገና በማድጋ ብለህ ፮ ጊዜ ድገም ፍቱን ውእቱ።

 

 

         ሐራ ወርኅ ስም ወርኅ ወንጌላዊ በ፲፪ ግደፍ

 

      ፩፤ በአልታሰበ ነገር ገንዘብ ታገኛለህ ነገር ግን ጠብ አታንሣ ባላጋራም ቢነሣብህ ወደ እግዚአብሔር ለምን እዘን ይጠፋልሃል ሰው በመላሱ ይነዳሃልና አትከተለው ባሕቱ ተዓገሥ ወአፅንዕ ልበከ ወተሰፈዎ ለእግዚአብሔር ጭዳው ቀይ በግ ነው ፊትህን ወደ ምዕራብ አድርገህ እረድ ቀንዱን ከጠጉሩ ጋር ታጠን ከሰሉን ለነፋስ ሰጠው።

 

      ፪፤ ደስታ ነገር ታገኛለህ መልአከ ውቃቢህ አይለይህም ከዝሙት ተለይ ሕማም እንዳያገኝህ እስከ ፰ ቀን ተዓቀብ መንገድ ርቀህ አትሒድ እምድኅረዝ አልቦ ፀር ጭዳው ቀይ በግ ነው፤ ፊትህን ወደ ምሥራቅ አድርገህ እግዚአብሔር ነግሠን ደግመህ እረድ፤ ልብህ ያሰበውን ነገር ሁሉ ታገኛለህ ይሆንልሃል።

 

      ፫፤በቤትህም በእዳሪም ብርቱ ምቀኛ አለብህ ይነሣብሃል ለነፍስህ ክርምንዮስ ጼቃ ቤቃ የውጣ ሳዶር አላዶር ዳናት አዴራ ሮዳስ ዝበግዕ መጽአ ለተጠብሖ ከመ ይቤዙ ወያድኅነ ኵሎ ዓለመ ከማሁ አድኅነኒ እምጸብአ ፀላኢ ወፀር ለገ እገጭዳው ነጭ በግ ነው፤ ደሙን በዕቃ ተቀብለህ ፪ ጊዜ ደግመህ በወረቀት ጽፈህ ደሙን ጭምር በጉድጓድ ቅበር።

 

      ፬፤ትልቅ ደስታ ነው ነገር ግን ከቤትህ ሰው ይሞታል። ነገር ይነሣብሃል አንተ ትመወእ፤ ግፍዖሙን ፫ ጊዜ ድገም፤ ፊትህን ወደ ምዕራብ አድርገህ ጥቁር ፍየል እረድ ጠላትህ ሁሉ ይታገሣል አደራ አትቀበል። እስከ ፲፪ ቀን ተዓቀብ።

 

      ፭፤ መልካም ነው ከቤተ መንግሥት ብትገባ ነገርህ ይቀናል ጭዳው ቀይ በግ ነው። ጐሥዐ ልብየን በትረ ጽድቅ ወበትረ መንግሥትከ እስካለው ድረስ ፯ ጊዜ ድገም። ደሙንና ቅብዓ ቅዱሱን አንድ ላይ አድርገህ በትምእምርተ መስቀል ቅበዕ ገጸከ፤  ከጌታህ ቤት ብትሔድ ይቀናሃል፤ ፊትህን ወደ ምሥራቅ አድርገህ እረድ።

 

      ፮፤ደም ያስፈልግሃል ክፉ ነገር ያገኝሃል መንፈስ ርኩስ ያስፈራሃል ከበሸታ ተጠነቀቅ አንድ ዘንድ ሁነህ ቤተክርስቲያን ሳም። እግዚኦ ኢትጸመመኒን ፯ ፯ ጊዜ ማለዳ ማለዳ  ድገም። እስከ ፲፩ ቀን ተዓቀብ። ከጥቁር ሴት ጋር አትተኛ ጭዳው ቀይ በግ ነው ከደሙ በራስህ አሳልፈህ ወደ ኋላህ በግራ እጅህ እርጭ።

 

      ፯፤ ወላውል ክፉም መልካምም ነው፤ ኃዘንም ደስታም ነው፤ ለገንያ ለመንገድ ደግ ነው። ቀይ ሴት ምክንያት ሁና መልካም ሥራ ታያለህ፤ ነገር ግን ትንሽ ሕማም ያምሐል። ፯ ቀን ተዓቀብ ጭዳው ነጭ በግ ቢገኝ ከብት አለዚያ ፍየል እረድ ፤ ከፈራኸው ሁሉ ትድናለህ።

 

      ፰፤ ጠላት ይነሣብሃል አትፍራው በእጅህ ይወድቃል። እስከ ፲፩ ቀን  ተዓቀብ፤ ጭዳው ጥቁር በግ ነው። ራሱን በቤትህ አዙረህ ቅበር ጠላትህ ቢሆን ይሞታል ባይሆን ዙሮ በጅህ ይወድቃል።

 

      ፱፤ሠናይ ከንጉሥ ቤት ለመግባት ከተማ አትልቀቅ ሹመት ሽልማት ታገኛለህ። ነገር ግን ከፈረስ ላይ አትቀመጥ ትወድቃለህ። እሰከ ፲፱ ቀን ተዓቀብ ጭዳው ቀይ በግ ነው ፀሐይ ስትወጣ ረድ፤ ከደሙ ቅመስ።

 

      ፲፤ የሴት ጠብ ይነሳብሀል፤ በእጅህ አትንካት ትሞትብሀለች ደም ያስፈራሃል ተጠንቀቅ ልብ አድርግ፤ ጭዳው ቀይና ነጭ በግ ነው። እስከ ፱ ቀን ተዓቀብ።

 

      ፲፩፤ ገንዘብ ታገኛለህ፤ ውሻ ይነክስሃል አትበሳጭ፤ እግዚአብሔር ይጣላሃል ልብ አድርግ። ከሌባ ተጠንቀቅ ከሴትም አትጣላ፤ ጭዳው ነጭ በግ ነው። እስከ ፯ ቀን ተዓቀብ።

 

      ፲፪፤ ያገር ሰው ሁሉ አሲሮ ይነሳብሃል፤ ክፉ የጠና ምክር ይመክርብሃል። ያስፈራሃልና ተጠንቀቅ እስከ ፳፩ ቀን ተዓቀብ፤ ጭዳው ጥቁር ፍየል ነው። ሚራጊ ኑዊል ሚሮን ዐማኑኤል ፓፓሮስ ኢያኢል ዘኑኵኵታኢል ኢልማስ ያሩስማሄል ኢል ኢልታዲራ ማዲራ ምያሮምስ አርሳኤል ራኢል ኢያኢል ዳኢል በእሉ አስማት ከዓው ከመ ማይ ወአድክም ኀይሎሙ ለፀርየ ወለጸላእትየ ለገብርከ እገ ብለህ ፯ ጊዜ በዕለት ዉሀ ላይ ደግመህ አፍስስ።

 

 

                          74

 

         ሀሳበ ሙግት። ስም ዕለት ሌሊት በ፱ ግደፍ።

 

      ፩፤ ነገር ይበዝኅ ፪፤በግራ በኩል ቁም። ፫፤ ክፉ ነው ኢትጻእ እምቤትክ። ፬፤ ጥቀ ሠናይ ተሟገት። ፭፤ ዳኛው ያደላብሃል እንዳሻህ አትናገር። ፮፤ እኩይ ኢትሑር። ፯፤ ነገር ተው። ፰፤ እርቅ ነው ኢትፍራህ። ፱፤ ሙግት በነግህ እርቅነው።

 

                          75

 

            ሀሳብ ሰጐን ወደንቃራ ዘመን ስም ወእ

 

          ም ዓመተ ምሕረት ወንጌላዊ በ፲ ግደፍ።

 

      ፩፤ አንተ ሰው እጅግ አትደንግጥ ክፉ ሕልም ታያለህ በዚህ ዘመን የተመኘኸውን ታገኛለህ። ችግርህ ይቃለልልሃል መልካምከመጣ በህውላ ኃዘን ያገኝሃል። ተመልሰህ መልካም  ታገኛለህ፤ ፀር ይወድቅ ለከ ንግድ እርሻ ሁሉም ነው። በሽታህ ሴት ዛር አይታሃለች በዓይኗ ቀይ ሴት ፍየል ውይም ነጭ ፍየል እረድ። ተሐዩ በነጭ ቦታ ንበር።

 

      ፪፤ አንተ ሰው አትፍራ መልካም ነገር ይመጣልሃል በሽታህ በገላህ ተናኝቷል፤ በመላስህ ባትነካው ደዌህ አያድርብህም በግምባሩ ነጭ ያለበት ፍየል እረድ። ባይሆን በግ እረድ። ለከብት ለቦታ ለንግድ ደግ ነው። እግዚአብሔር ቢረዳህ ንብረትህ አይጠማም።

 

      ፫፤አንተ ሰው በዕድሜ ታይላለህ፤ ያሰብኸውን ታገኛለህ፤ እመን በእግዚአብሔር ጥቂት ንግድ ይቀናሃል ከቤትህ ይመጣል። በሽታህ ጋኔን አይቶሃል ጥቁር በግ እረድ ያፈርሀከ። ኋላ መንቆር ኖታ ትኖራልሀ ሐሪስ ነጊድ ቤተ ንጉሥ ይሤኒ ለከ ጐረቤትህ ያስብልሃል ምቀኛህ ብዙ ነው ግማሽ ገላህን ያምሃል ፍራው።

 

      ፬፤ አንተ ሰው በዚህ ዘመን እዘን በልብህ በብዙ የሚረባ ነገር ይመጣልሃል፤ በአንተ ላይ ዕውቀት አለህ ይልሃል፤ እጅግም ኃዘን አያገኝህም ይልሃል፤ ዘወትር ሁሉም ይሆንልሃል በሽታህ ሴቶች ዛሮች አይተውሃል፤ ቀይ ፍየል ይነሳሉ አርደህ በደሙ ታጠብ።ሹመት ታገኛለህ፤ በቀይ ዶሮ አርደህ በልተህ ለእርሻ ሑር ብሔረ ባዕድ ተኅሥሥ፤ ሥዕለት ይሠምር ለከ።

 

      ፭፤አንተ ሰው በዚህ ዘመን ያሰብኸው አይሆንም፤ ተጠንቀቅ። ጥል አታንሣ ቀንህ አይደለምና እንደ እሳት የሚገለጥ ደዌ ያገኝሃል፤ ጋኔን ያይሃል፤ ጥቁር ፍየል አው ደንግላ በግ እረድ።

 

      ፮፤አንተ ሰው የተመኘውን ታገኛለህ፤ ጥበብ አለ፤ መልካም ነው፤ ከብትህ ይበዛል፤ ጠላት ምቀኛ አለብህ፤ ይጠፋል። ግን በጥቁር ሰው የተነሣ ነው፤ በዋስነት በሰው ነገር ትጠፋለህ። እርሱ ካለፈ አትፍራ ምንም የለብህ ንብረትህ መልካም ይሆናል፤ የክፉ ሰው ዓይን አይቶሃል፤ ወንድ ነጭ በግ እረድ።

 

      ፯፤ አንተ ሰው የተመኘኸውን ታገኛለህ፤ አሩትህ ደግ ነው። ብትገዛም ጐዳናም ንግድም ሁሉም መልካም ነው፤ ከጋኔን የተወለደች ነጭ ባልቴት ዛር አይታሃለች፤ በልብህ በከርህሥ በራስህ ትገባለች፤ ቀይ ፍየል እረድ ሰባት  ወደ ላይ ስድስት ወደታች ሆኖአል ተጠንቀቅ።

 

      ፰፤ አንተ ሰው በርሱ የተወጋህ የቻልህ እንደሆን መልካም ነገር ይመጣልሃል ንግድ ሠናይ ለከ ይወድልሃል ሌላ ሲሳይ ታገኛለህ በሽታህ ቀይ ዛር ናት አስደግማብሃለች፤ ቀይ ወይም ጥቁር ፍያል እረድ ተሐዩ ቦታህም  ጥጋጥግ ነው፤ ሰላቢ ይፈታሃል።

 

      ፱፤ አንተ ሰው  ይኸ ዘመን ክፉ ይሆንብሃል ምቀኞች አሉብህ እዘን አትርሱኝ በል ፀሎት አስይዝ፤ ምጽዋት ስጥ፤ ፈጣሪህ ይረዳሃል፤ ምንም ቢሆን ልጅ ትወልዳለህ ነገሩ ሁሉ ይቀናሃል በጫማህ የሚሠፍር አለብህ፤ በሽታህ ከልጅነትህ ነው፤ ጋኔን አይቶሀል፤ ነጭ ፍየል እረድ ፈጣሪህ ያድንሃል

 

      ፲፤ አንተ ሰው ይህ ነገር ማየት መልካም ነው ፍርሀት ይረክበከ ምፅዋት ስጥ ያሰብኸው ይሆንልሃል፤ ደስታ ነገር ታገኛለህ፤ እሩቅ ብትሄድ በደህና ትመለሳለህ። በሽታህ እንደ ነፋስ ሽው ያለ ነው፤ ጋኔን አይቶሃል ስጥቅማ ፍየል እረድ። ሰው ሲከት ለራት ይሆናል። ራሱን ቆርጠህ ከአውራ መንገድ ቅበር ለበረከትም ለራትም ይሆናል  መርሕ ነው፤ ምቀኛህ ያርፍልሃል፤ ፍየል ደግ ነው፤ ከሹም ደስታ ታገኛለህ እሩቅ መንገድ ብትሔድ በደኅና ቶሎ ትመለሳለህ።

 

                          76

 

   ሀሳበ መናዝል ኮከብ ስም ወእምዓመተ ምሕረት ወንጌላዊ ፲

           እምኅበ አልቦ ወስክ በ፳ ወ፰ ግደፍ።

 

      ፩፤እኩይ እስከ ዓመት ተዓቀብ፤ ወአፍትን ርእሰከ ዳዊትኒ ተነበየ ወይቤ ወደእንተዝ ይትነሥኡ ራሲዓን እምደይን። ፪፤ ሠናይ ትረክብ ኦ ብእሲ ሢመት ተዓቀብ ጸላእትከ ይመውቱ ዳዊትኒ ይቤ  እግዚኦ ሚበዝኁ እለ ይሣቅዩኒ።፫፤ እኩይ  እሰክ ፰ ወርኅ ተዓቀብ፤ ይሬእየከ ሞት ዳዊትኒ ይቤ እብዚኦ ሚበዝኁ እለ ይሣቅዩኒ። ፬፤ ሠናይ ይከውን ዘሐለይከ ዳዊትኒ ይቤ ተፈሥሑ ጻድቃን በእግዚአብሔር። ፭፤ ሕማሞ በአባልከ ወደዌ በዓይንከ ዳዊትኒ ይቤ ይነብብ ኃጥ በዘያስሕት ርእሶ። ፮ ወ፯ እኩይ ተዓቀብ ዳዊትኒ ይቤ እግዚኦ በመዓትከ ኢትቅስፈኒ። ፰፤ ፍሥሐ በኵሉ። ዳዊትኒ ይቤ እግዚኦ ኵነኔከ ሀቦ ለንጉሥ። ፱፤ ሓዘን ወምንዳቤ ወጥፍኣት ተዓቀብ። ዳዊትኒ ይቤ እገኒ ለከ እግዚኦ በኵሉ ልብየ። ፲ እኩይ በኵሉ ዳዊትኒ ይቤ በእግዚአብሔር ተወከልኩ እፎ ትብልዋ ለነፍስየ።፲ወ፩ ቅድመ ፍሥሐ ወድኅረ ሓዘን ተዓቀብ ዳዊትኒ ይቤአድኅነኒ እግዚኦ ወተሣሀለኒ።፲ወ፪ ፲ወ፫ በእሉ ተዓቀብ ከመ ኢትሙት እንበለ ንስሓ ዳዊትኒ ይቤእስከ ማእዜኑ ዓዲ ይብል አብድ  በልቡ።፲፬ ሠናይ በኵሉ ዳዊትኒ ይቤ ብፁዓን እለ ተኃድገ ሎሙ ኃጢአቶሙ። ፲ወ፭ እኩይ ደዌ ወመከራ ተዓቀብ ዳዊትኒ ይቤ ዕቀበኒ እግዚአ። ፲ወ፮ ፲ወ፯ በእሉ እኩይ ትደዊ ጥቀ ትትነሣእ። ዳዊትኒ ይቤ ተንተንኩ  ለወዲቅ ወእግዚአብሔር አንሥአኒ።፲፰ ወዲቅ እምፈረስ ወበቅል ወመፍቅድከ ሕይወት ይከውን ለከ ዳዊትኒ ይቤ ይስማዕካ እግዚአብሔር በዕለተ ምንዳቤከ።፲፱ ፍሥሐ ወደክብር ሞገስ ወሢመት  ዳዊትኒ ይቤ ሣህልከ እግዚኦ ይርከበኒ ፍጡነ ፳ እኩይ እኪት ወሞት ወደዌ ሀሎ ተዓቀብ። ፳፩ ፍሥሐ ፈሬ ሰላም በረከት በኵሉ ዳዊትኒ ይቤ እግዚአብሔር ይሬእየኒ ወአልቦ ዘየኃጥአኒ ፳ወ፪ ሣህል ወምሕረት ወሢመት ዳዊትኒ ይቤ ለእግዚአብሔር ምድር በምላዓ። ፳፫ ሕማም ያበጽሐከ ለሞት ተዓቀብ ዳዊትኒ ይቤ ኀቤከ እግዚኦ አንቃዕዶኩ አምላኪየ። ፳፬ ሠናይ በ፲ሩ ወርኅ እኩይ ተዓቀብ ዳዊትኒ ይቤ አንሰ በየውሐትየ አሐውር ፳፭ ትደዊ ወተሓዩ ወሢመት ሀሎ ፀር ይትሀሣእ ወይትኃፈር  ዳዊትኒ ይቤ እግዚአብሔር ያበርህ ሊተወያድኅነኒ ምንትኑ ያፈርሐኒ። ፳ወ፮  እኩይ በኵሉ ዳዊትኒ ይቤ እግዚኦ ኢትጸመመኒ ሰእለትየ። ፳ወ፯  ሠናይ  ፍሥሓ በ፲ወ፪ ወርኀ ተዓቀብ እኩይ ወእቱ።፳፰ ሰላም ወጥዒና በኵል ጸሎት ወምጽዋት።

 

 

                          77

 

 

         ዓውደ ፀሕይ በዘተአምር ባተሎ ሠናየ ወኢኩየ ስም ወእማአመተ

          ምሕረት ውንንጌልዊ በዓተ ዩኢሐንስ ዕለት በ፳ወ፱ ግድደፍ።

 

      ፩፤ እኩይ እሰከ ፭ ወርኅ ተዓቀብ ሹም ይእኅዘከ ወይሞቅሐከ ወይትበአሱ አዝማዲከ ወእሳት ያውዒ ቤተከ በ፩ ቦታ ኢትንበር። እስከ የካቲት ተዓቀብ ወድኅረ ሠናይ። ፪፤ ኢትሑር ኀበ መኰንን በጥር። ይሞቅሐከ ወይነሥእ ንዋየከ በምክንያት እስከ ጥር ተዓቀብ ወድኅረ ሠናይ። ፫፤ እኩይ ውሉድከ ይመውቱ አንተ ወብእሲትከ ትትሓመሙ በግንቦት ለእመሖርከ መንገለ ምሥራቅ ረሃብ ብከ በሰኔ በነሓሴ ተዓቀብ ፬፤ ሠናይ ገራሕት ይሠምር ነጊድ ይረብሕ ያውዒ እሳት ቤተከ በጥር በግንቦት ተዓቀብ። ፭፤ ሠራቂ ይነሥእ ንዋየከ ወከልብ ይነስከከ እግረከ በሚያዝያ ተዓቀብ ወድኅረ ሠናይ።፮፤ ኅድግ ቦታከ ኀበ ካልእ ትረክብ ዘፈቀድከ ወትሰየም ወይሰማዕ ዜናከ ከመ ድምፀ ባሕር ወኢይክል መኑሂ ይትቃረነከ ሠናይ ለከ።፯፤ እኩይ መሠርይ ይትቃረነከ ጕየይ ኀበ ካልእሀገር ደም ይውኅዝ ላዕለ ብእስቲከ በጥቅምት በግንቦት ተዓቀብ። ፰፤ እኩይ ንዋይ ይጠፍእ ውሉድ ይመውቱ መኰንን የኃሥሠከ በሰኔ ተዓቀብ። ፱፤ ሠናይ በኵሉ። ፲፤ ንበር አልቦ ተፋልጦ እምዮሐንስ እስከ ዩሐንስ።፲፩፣ ፲፪፣፲፫ ድምር ውእቱ ።፲፬ ማእከለ ባሕር ይሠጥመከ ወመብረቅ ይትኄየለከ ዘሓመ ኢይትነሣእ ወዘውጽኦ ኢይገብዕ አፍትን ርእሰከ ለካህን። ፲፭፤ ሠናይ ንዋየ ትረክብ በዝሙት ትነድድ ወትቆርር በንዋይ። ፲፮፤ እኩይ በጥር በየካቲት በመጋቢት ተዓቀብ ከመ። ኢትሙት በኵናት ደዔ ወጋኔን በልብከ ያፈርሐከ ኢብዝኅ  ሜሰ ወዕቁባተ።፲፯፤ ሠናይ ለርእስከ ባሕቱ ብእሲትከ ትትሓመም ባርያ ይእኅዛ ወእንዝ ትትሓጻብ ሕልፃ ተሐዩ እሞት በጥር በየካቲት በመጋቢት ትዓቀብ እምዝሙት። ፲፰፤ ኢትጻእ እምቤትከ በ፬ መንበር ኢትንበር ተዓቀብ በግንቦት። ፲፱፤ ነጊድ ወሐርስ ይሠምር ለከ ወኵሉ ግብር ይትባረክ በሚያዝያ ንስቲት ደዌ ይረክበክ ተዓቀብ። ፳፤ ሥዩም ያፈቅረከ ንዋየ ታጠሪ ውሉድከ ይበዝኁ እሳት ወደዌ ይትኄየለከ በሰኔ ተዓቀብ። ፳፩፤ ሥራይ ይትኄየለከ ኢትኩን መዓትመ ብእሲትከ ዘወለደቶ ይመውት ወለእመ ወለደት አልቦ ዘይበቁዕ እምባዕድ ባቁዐ ይከውን ብዙኃ ተዓቀብ እስከ ሚካኤል በውእቱ መዋዕል እሰከ ሰኔ ተዓቀብ። ፳፪፣፳፫፣፳፬፣፳፭ ለእመ ይከውን ኢትንበር በቀዳሜ ቤትከ ተስፋ አልብከ ጹም ወጸሊ ወትረ ወእመ ወለድከ ትደዊ ተዓቀብ እምባዕድ ኢታብዝ ዕቁባተ። ፳፮፤ ኢትኩን መዓትመ በዝመዋዕል በእዴከ ሰብእ ይመውት ተዓቀብ  ደዌ ይትቃረነከ ወእኪት ይመጽአከ። ፳፯፤ ሰራቂ ይትቋረነከ መሠርያን ይእኅዙከ ላፂ ላፂ ወቅረጽ አጽፋረከ ወዘፈረ ልብሰከ ወንሣእ መሬቱ እማዕከለ ፍኖት ወጋጋ ቀንድ አውዒ በእሳት ደሚረከ በመስከረም በጥቅምት በኅዳር በጥር በመጋቢት በሚያዚያ በግንቦት በሐምሌ እሎንተ ዕቀብ።፳፰፤  ሠናይ ትፍሥሕት ወኃሤት ባሕቱ በሚያዚያ በ፰ ቀን ዓይነከ ትትሐመም ተዓቀብ። ፳፱፤ በኵሉ ሠናይ ፍሥሐ ይከውን እምዮሐንስ እስከ ዮሐንስ ተፈፀመ ሓሳበ መናዝል በዕውነት ያለሐሰት።

 

                  ————————-

 

 

 

                         መድኃኒቶች 

 

፩ኛ፤ ለደም ብዛት ቀይ ሽንኩርት ክትፎ በውሀ ዘፍዝፎ በንጹሕ ጨርቅ አጥሎ በሲኒ እየለኩ ጧት በባዶ ሆኑ መጠጣት ነው።

 

፪ኛ፤ የችፌ በሽታ በሰውነት ላይ ይቆስላል እገዞ እየተንጠባጠበ ያሰቃያል የዚህ መድኃኒት የክትክታ ቀንበጦች ለጋዎቹ  በእሳት አሳርሮ በቅቤ ለውሶ መቀባት ነው በሽተኛው በጥቂት ቀን ይፈወሳል።

 

፫ኛ፤ ለሆድ ቁርጠት ነጭ ዕጣን ሁለት ሦስት አንኳር ማኘክ ነው በቶሎ  ይፈወሳል።

 

፬ኛ፤ ማር ወተትና ቅቤ በዕድሜ የቆዩ ቢመገቡት ሰውነታቸው ይጠነክራል ጤናማ ይሆናሉ።

 

፭ኛ፤ ሽማግሌዎች የወይራ ዘይት በምግብነትም ሆነ ሕመም በሚሰማው ቦታ በማድረግና ጥሩ ውኃ በመጠጣት ዐይን ጆሮ በታመመ ጊዜ የወይራ ዘይት ቢቀባ ይድናል።

 

፮ኛ፤ ነጭ ሽንኩርት ፈዋሽ መድኃኒት ነው ነጭ ሽንኩርት ምግብን አጣርቶ ጤንነትን ይሰጣል በአንጀት የሚከማቸውን ቆሻሻ ያስወግዳል። በኩላሊት ያሉትን ያጣራል ሌሎችንም በሽታዎች ይፈውሳል ስለዚህ ከ፩ እሰከ ሁለት ፍሬ ከቁርስ ወይም ከምሳ ጋር መመገብ ነው።

 

፯ኛ፤ ለላሽ መድኃኒት ከራስ በሚወጣው ኵስሕ ለራስ መቀባት ነው ፍቱን መድኃኒት ነው።

 

                  —————————-

ዳውንሎድ ሞባይል አፕ

ሶሻል ሚድያ ላይ ያግኙን

 

Copyright © 2010 – 2023 zetewahedo.com | All rights reserved.
error: Content is protected !!
Scroll to Top