ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ ነው እዚህ በመጫን ያንብቡ

ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው እዚህ በመጫን ያንብቡ

 ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን የተነገሩ ምሳሌዎች እዚህ በመጫን ያንብቡ

ኢየሱስ ፈራጅ ወይስ አማላጅ?

በ1938 ዓ.ም የታተመው መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል ፦ “ክርስቶስ ኢየሱስ ሞተ ከሙታንም ተለይቶ ተነሳ በአብ ቀኝ ተቀምጧል ስለ እኛ ይፈርዳል”። በ1975 ዓ.ም ከግዕዝ ወደ አማርኛ የተተረጎመውም እንዲህ ይላል፦ “የሚፈርድ ማን ነው? ክርስቶስ ኢየሱስ ሞተ ከሙታንም ተለይቶ ተነሳ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጧል ስለእኛም ይፈርዳል።”
በአሁኑ ሰዐት ከኦርቶዶክሳውያን በቀር በአብዝሃኛው ሕዝብ ተሰራጭቶ የሚገኘው እንዲህ ይላል፦ “እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው:: የሚኮንንስ ማን ነው? የሞተው ይልቁንም ከሙታን የተነሳው በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው ደግሞ ስለኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።” በሮሜ 8:-34 ላይ በተለያዩ ዘመናት የተጻፉ መጽሐፍ ቅዱሶችን ተመልክተናል። ቀድሞ የታተመው መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለኛ ይፈርዳል ብሎ ፈራጅ ሲያደርገው በብዙወቻችን እጅ አሁን የሚገኘው አዲሱ ትርጉም አማ ላጅ አድርጎታል። ታዲያ ትክክለኛው የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የትኛው ነው? ብለን ስንጠይቅ መረዳት የምንችለው አንድም ቀዳሚውን በመመልከት ካልሆነ ደግሞ ከምንባቡ ሃሳብ በመነሳት ነው። ስለዚህ ቀጥለን በዝርዝር እንመልከተው። ቁጥር 33 ላይ እንዲህ ሲል ይጀምራል:-“እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል?” ይህ ማለት እግዚአብሔር ተከተሉኝ ብሎ በመጥራት የመረጣቸውን አይ እነርሱ አያስፈልጉንም ፣ አንተን ሊከተሉ አይገባቸውም ብሎ የሚከሳቸው ማን ነው? በማለት ይጠይቃል በመቀጠልም “የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።” በማለት የመረጣቸውን ሰዎች መንግሥቱን ለማውረስ እናንተ የአባቴ ብሩካን የሚያጸድቃቸው እግዚአብሔር ነው አለ፤ እንዲሁም የሚኮንን (የሚፈርድ) ማን ነው? በማለት ይጠይቃል። “መኮነን” ከግዕዙ ሳይተረጎም ቀጥታ የተወሰደ ቃል ሲሆን “ መኮነን“ ማለት መፍረድ ማለት ነው። ምክንያቱም “ኮነነ” ከሚለው የግዕዝ ሥርዎ ቃል የወጣ ነው። “ኮነነ” ማለት ደግሞ ፈረደ ፣ ገዛ ማለት ነው።እንግዲህ ማጽደቅና መኮነን የተለያዩ ትርጉም እንዳላቸው ማስተዋል ያስፈልጋል። ካፈርኩ አይመልሰኝ ካልሆነ እውነታው ይህ ነው። ማጽደቅና መኮነን የአማላጅነት ሥራ ሳይሆን … ተጨማሪ ያንብቡ ︾

የኢየሱስ ክርስቶስ ታሪክ፦

የጌታችን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ ታሪክ የምናጠናው በአራቱ ወንጌላት አቀራረብ መሠረት ነው። ስናጠናም የታሪኩን ቅደም ተከተል በመጠበቅ ይሆናል።
የኢየሱስ ክርስቶስ ቀዳማዊነት፦
ከአራቱ ወንጌላት ውስጥ የኢየሱስ ክርስቶስን ቀዳማዊነት በመተረክ የሚጀምረው የዮሐንስ ወንጌል ነው። ቀዳማዊነት ስንል ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የነበረ፤ አልፋና ዖሜጋ፤ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው፤ ሁሉ በእርሱ የሆነ፤ ማንም የማይቀድመው፤ ለዘመኑ ጥንት ወይም ፍጻሜ የሌለው ማለታችን ነው። በዚሁ በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ተጽፎ የምናገኘው ታሪክ ገና ከመግቢያው ሲል እንዲህ ሲል ይጀምራል፦ በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። በእርሱ ሕይወት ነበረች፥ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረች። ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም። ዮሐ. ፩፡ ፩ በዚህ ክፍል ዮሐንስ ጌታን <ቃል> ብሎ ይጠራዋል። ይህም በግሪክኛ <ሎጎስ> ይባላል። የኢየሱስ ክርስቶስ ህልውና የሚጀምረው በቤተልሔም ከተወለደ ጀምሮ አይደለም። ነገር ግን ዓለም ከመፈጠሩ በፊት በአምላክነቱ (በእግዚአብሔርነቱ)….ተጨማሪ ያንብቡ ︾

 አልተሳሳትንም ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው

 መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ

ብዙዎች በዘመናችን የመጽሐፍ ቅዱስን ትምህርት ባለመረዳትና “እኔና አብ አንድ ነን” ያለውን የአምላካቸውን የኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክነትን፣ ፈጣሪነት፣ ፍጹም ተዋሕዶውን ፈራጅነቱን በመካድ ሎቱ ስብሐት ከአብ አሳንሰው ርሱን ለማኝ አብን ተለማኝ ያደርጋሉ፤ ቅድስት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ከበፊት ጀምሮ እስካሁን ከመናፍቃን የሚደርስባት ፈተና ለምን ኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክ ነው? ለምን ከአባቱ ጋር የተካከለ ፈራጅ ነው? ብለሽ ታስተምሪያለሽ የሚል ነው፤

ይህም ዐዲስ አይደለም የባሕርይ አምላክነቱን፣ ተዋሕዶውን፣ ፈራጅነቱን ከካዱት ውስጥ ከቀድሞዎቹ እነ ጳውሎስ ሳምሳጢ፣ አርዮስ፣ ንስጥሮስ …. በ16ኛው መቶ ክ.ዘመን ወዲህ በየዘመናቱ የሚነሱ የእምነት ድርጅቶች ወ.ዘ.ተ ይገኛሉ፤ የእነዚኽን አስተምህሮ በማስተምርበት የነገረ መለኮት ኮሌጅ ውስጥ ከደቀ መዛሙርት ጋር በክፍል ውይይት ጊዜ በጥልቀት የምዳስሰው ቢኾንም፤ ለ ፌስ ቡክ (face book) ጓደኞቼ ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የምታስተምረውን በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጻፈውን አስተምህሮ ጥቂቱን ከዚኽ በታች አስፍሬዋለኊ፡- ይኸውም በብሉይ ኪዳን የተጠቀሰው እግዚአብሔር ከሦስቱ አካል አንዱ እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለመኾኑ የተጻፈውን የብሉይ ኪዳንና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን እውነት በማንበብ አረጋግጡ፡-

ሀ) ኢየሱስ ክርስቶስ በእውነት እግዚአብሔር ነው እንላለን፡፡

►“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ” (ዘፍ 1፡1) ╬ “ጌታ ሆይ፥ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ ሰማዮችም የእጆችህ ሥራ ናቸው” (ዕብ 1፡10)

►“እግዚአብሔርም ሙሴን፦ «ያለና የሚኖር» እኔ ነኝ አለው እንዲህ ለእስራኤል ልጆች። «ያለና የሚኖር» ወደ እናንተ ….ተጨማሪ  ያንብቡ

ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ ስለመባሉ ከሌሎች ሐዲሳት እነዚህ ክፍሎች ይጠቁሙናል፦

􀂾 እንግዲህ ይህን እናንተ የሰቀላችሁትን ኢየሱስን እግዚአብሔር ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ። የሐዋ. ፪፡፴፮፤
􀂾 ወዲያውም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በምኵራቦቹ ሰበከ። የሰሙትም ሁሉ ተገረሙና። ይህ በኢየሩሳሌም ይህን ስም የሚጠሩትን ያጠፋ አይደለምን? ስለዚህስ ታስረው ወደ ካህናት አለቆች ይወስዳቸው ዘንድ ወደዚህ አልመጣምን? አሉ። ሳውል ግን እየበረታ ሄደ፥ በደማስቆም ለተቀመጡት አይሁድ ይህ ክርስቶስ እንደ ሆነ አስረድቶ መልስ ያሳጣቸው ነበር። የሐዋ. ፱፡፳-፳፪
􀂾 ሲተረጉምም ክርስቶስ መከራ እንዲቀበልና ከሙታን እንዲነሣ ይገባው ዘንድ እያስረዳ። ይህ እኔ የምሰብክላችሁ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ ነው ይል ነበር። የሐዋ. ፲፯፡፫
􀂾 የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና። ሮሜ. ፲፡፬
􀂾 እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ይህም ለአይሁድ ማሰናከያ ለአሕዛብም ሞኝነት ነው ለተጠሩት ግን፥ አይሁድ ቢሆኑ የግሪክ ሰዎችም ቢሆኑ፥ የእግዚአብሔር ኃይልና የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነው ክርስቶስ ነው። ፩ቆሮ. ፩፡፳፫-፳፬
􀂾 ክርስቶስ አይደለም ብሎ ኢየሱስን ከሚክድ በቀር ውሸተኛው ማን ነው? አብንና ወልድን የሚክድ ይህ የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው። ፩ዮሐ.፪፡፳፪
􀂾 ክርስቶስ ነው ብሎ በኢየሱስ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዶአል፥ ወላጁንም የሚወድ ሁሉ ከእርሱ የተወለደውን ደግሞ ይወዳል። ፩ዮሐ. ፭፡፩
ኢየሱስ እርሱ የሰው ልጅ (ፍጹም ሰው) ነው።
የሰው ልጅ ስለመባሉ ከማቴዎስ ወንጌል እነዚህ ክፍሎች ይጠቁሙናል፦
􀂾 ኢየሱስም ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይም ወፎች መሳፈሪያ አላቸው፥ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም አለው። ማቴ. ፰፡፳
􀂾 ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። ማቴ. ፲፮ ፡፲፫።
የሰው ልጅ ስለመባሉ ከማርቆስ ወንጌል እነዚህ ክፍሎች ይጠቁሙናል፦
􀂾 የሰው ልጅ ብዙ መከራ ሊቀበል፥ ከሽማግሌዎችም ከካህናት አለቆችም ከጻፎችም ሊጣል፥ ሊገደልም ከሦስት ቀንም በኋላ ሊነሣ….ተጨማሪ ያንብቡ ︾

በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ

 1ጢሞ.2:5 “አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤”

ይህ ምን ማለት ነው? አንድ እግዚአብሄር አለ ሲልስ ምን ስለማለት ነው? መካከለኛስ ሲባል እንዴት ነው?

የተወደደ አባታችን ቅዱስ ጳውሎስ << አንድ እግዚአብሄር አለ>> ይለናል ፤ ይህም አንዳንዶች ጣኦት አምላካውያን ብዙ እንደሚያደርጉት ያይደለ <<አንድ>> ብቻ አምላክ እርሱም እግዚአብሄር እንደሆነ ይነግረናል፡፡ ይህን ቅዱስ ጳውሎስ ሲጠቅሰው በእዉኑ ስለአንድ አምላክነት ሲገልፅ እንጂ ከልጁ አንፃር ነውን? አይደለም ፡ ምክንያቱም ልጁ ራሱ ክርስቶስ እግዚአብሄር አይደለምን?

<<በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ>> ይህስ ስለልጁ ስለክርስቶስ በግልፅ ይናገራል ፤ <<መካከለኛ>> እንዲሆን እግዚአብሄር ሰወች ሁሉ ይድኑ ዘንድ መውደዱን ለማረጋገጥ አንድያ ልጁን (ክርስቶስን) ወደ አለም ልኮታልና ፤ እግዚአብሄር አንድያ ልጁን ላከ ሲባል እንደምንድን ነው? አንድያ ልጁ ራሱ እግዚአብሄር አይደለምን? አስቀድመን እንዳልን ክርስቶስ ራሱ እግዚአብሄር ነው፡፡

1) እንግዲህ መካከለኛነት ስለወልድ ስለምን ተጠቀሰ? የክርስቶስ መካከለኛነት ዋና ተግባር <<ማስታረቅ>> ነው ፤ ማንን ከማን ለማስታረቅ ብንል ፦ እግዚአብሄርን ከሰው ጋር ለማስታረቅ፡፡ እንግዲህ እግዚአብሄርና ሰው ስለምን አስታራቂ አስፈለጋቸው? ምክንያቱም ሰው ራሱን ያስታርቅ ዘንድ በቅቶ አልተገኘምና እግዚኣብሄርም ራሱን ከሰው ጋር ያስታርቅ ዘንድ ይህን ሊቀበል የሚችል ሰው አላገኘምና ፤ ስለዚህም አስታራቂ አስፈለገ፡፡

2) አስታራቂ ለማስታረቅ ከየትኛው ወገን መሆን አለበት? ከሁለቱም ወገኖች ቀረቤታ ሊኖረው …. ተጨማሪ ያንብቡ ︾

“መዳን በሌላ በማንም የለም” /ሐዋ. 4፥12/

በመጀመሪያ ቃሉን ማን ተናገረው የት ቦታ ተናገረው መቼ ተናገረው በምን ምክንያት ተናገረው ብለን በደንብ ማየት ተገቢ ነው ቃሉን የተናገረው ሐዋሪያው ቅዱስ ጴጥሮስ ነው በመቅደስ ደጃፍ ከእናቱ ማህጸን ጀምሮ አንካሳ ሆኖ የተወለውን ምስኪን ቅዱስ ጴጥሮስ በናዝሪቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሳና ተመላላስ ባለው ጊዜ እግሮቹ ቀንተውለት ቆሙ የካህናት አለቆችና ሽማግሌዎች ጻፎች ሊቃነ ካህናቱም ሐና እና ቀያፋ ጴጥሮስ ዮሐንስንይዘው በምነ ሐይል ወይም በማን ስም ይህን አደረጋችሁ ቢሏቸው እናንተስ ሰቅላችሁ በገደላችሁት ነገር ግን ሞትን ድል ነስቶ በተነሳው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህንን አድርገናል ብሎ ጴጥሮስ መልስ ከሰጠው በኃላ መዳን በማንም የለም ብሎ እነርሱ የጠሉት እና የሰቀሉት ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ ራሱ አዳኝ መሆኑን ገለጸላቸው፡፡ቅዱስ ጴጥሮስ ና ሌሎችም ሐዋሪያት አላማቸው የኢሱስ ክርስቶስን ጌትነትና አዳኝነት መመስከርና ለዓለም ማሳወቅ ስለነበረ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና ብሏል ይህ ታዲያ ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ነው የሚያሰኝ ሳይሆን የስሙን መድኃኒትነት ክብር የሚገልጽ ነው፡፡ ‹‹መጽሐፍ ቅዱሳዊ መልስ መስጠት ጨዋነት ነው››.
ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር በሰራቸው ስራዎች ምን ተማርን የእርሱ ተከታዮች የሆንን ሁሉ የእርሱን አርአያ ልንከተል ይገባል ‹‹ከእኔ ተማሩ›› ብሎናል እና ልንማር ይገባል ማቴ 11፡29 ከእርሱ ብዙ እንማራለን ብዙ መማር የምንችለው አምላክ ፈጣሪ መሆኑን ስንረዳ ብቻ ነው፡፡ሐዋሪያት የጌታን ፈለግ ተከተሉ በድልም ተወጡ ዮሐ 15፡18-19 ,ዮሐ 16፡33 አርአያውን መከተል ሉቃ 2፡27 ,ሁሉን ነገር ጠይቀን መረዳት ሉቃ 2፡46 ,ስደትን አስተማረን ዮሐ 15፡2 እውነት እውነት እላችኃለው በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል፡፡እኔ ወደ አብ እሄዳለው አብም ስለ ወልድ እንዲከበር በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ አደርገዋለው፡፡ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ …. ተጨማሪ ያንብቡ ︾

ዳውንሎድ ሞባይል አፕ

ሶሻል ሚድያ ላይ ያግኙን

 

Copyright © 2010 – 2023 zetewahedo.com | All rights reserved.
error: Content is protected !!
Scroll to Top