ሥነ ፍጥረት (የዓለም አፈጣጠር)
እግዚአብሔር በስድስት ቀናት ውስጥ የፈጠራቸው ፍጥረታት በየወገናቸው ሲቆጠሩ ሃያ ሁለት ሲሆኑ :: በመጀመሪያው ቀን እሑድ የተፈጠሩት ፍጥረታት ስምንት ናቸው ::
1 ጨለማ 3 ውሃ 5 ነፋስ (አየር) 7 መላእክት
2 መሬት 4 እሳት 6 ሰባቱ ሰማያት 8 ብርሃን
ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደተፈጠሩ የሚታየውም ከማይታው እንደሆነ (እንደተፈጠረ) እናምናለን ። ዕብ 11 ፥ 3 በማለት ቅዱስ ዻውሎስ እንደተናገረ:: እነዚህም ዓለሞች የተባሉት (ዓለመ ምድር ፤ ዓለመ ሰማይ) ተብለው በሁለት ይከፈላሉ ።
ዓለመ ምድር
1 ጨለማ (ጊዜ) ፤ እግዚአብሔር በመጀመሪያ የፈጠረው ጨለማን ነው ።ጨለማን የፈጠረውም ከምንም (ካለመኖ ወደ መኖር አምጥቶ በአምላክነት ጥበቡ በማስገኘት) ነው ። እኛ ሰዎች አንድን ነገር ለመስራት ጥሬ ዕቃ የግድ ያስፈልገናል ከምንም ተነስተን ምንም ነገር መስራት አንችልም በዓለም ላይ የምናያቸው የሰው ልጅ ሥራዎች (ታሪካውያን መዛግብትና የሳይ ንሰ ውጤቶች) ሁሉ የተለያዩ ንጥረ ነገሮችን በማሰባሰብ የተሠሩ ናቸው ። ሰው ምን ቢያውቅ መሥራት የሚችለው ካለው ነገር ላይ ተጠቅሞ ነው ። እግዚአብሔር ግን ዓለማትን የፈጠራቸው (ያስገኛቸው) ያለምንም ነገር (እምኀበ አልቦ) ከምንም ነው ።
ይህም ጊዜ መቆጠር የተጀመረበት ሲሆን ፤ ሌሎቹ ፍጥረታት የተፈጠሩትም በጊዜ ውስጥ ነው ። ጊዜ ከመፈጠሩ በፊት ስለ ነበረው ሁኔታ ለሰዎች የማወቅ ችሎታ የላቸውም ። ሰዎች እንዲያውቁና እንዲመራመሩ የተፈቀደላቸው ከሥነ ፍጥረት በኋላ ያለውን ብቻ ነው ። ያንም ቢሆን የቻሉትን ያህል ይሞክራሉ እንጅ ሁሉንም ተመራምረው አይደርሱበትም ።
2 መሬት (ምድር)፤ በውስጡ ለሚገኙት ሁሉ መኖሪያ እንዲሆን የተፈጠረውና ከአራቱ ባህርያት አንዱ የሆነው መሬት ተፈ ጥሮው ከምንም ነው ። መሬት ብትን (አፈር) ሲሆን ፤ ምድር የተባለውና ዛሬ እንደምናየው የፀና የሆነው ከውሃ ጋር ተዋህዶ በመጠንከሩ ነው መሬት በዓይን ይታያል ፣ በእጅ ይጨበጣል ፣ በውስጡ ሶስት ባህርያት አሉት ።እነሱም ደረቅነት (የብስነት) ፤ ክብደት (ግዙፍነት) ፤ ጥቁርነት (ጽሉምነት) ፤ ናቸው ።
3 ውሃ ለፍጥረታት ሁሉ ሕይወት የሆነውና ከአራቱ ባህርያት አንዱ የሆነው ውሃ የተፈጠረው ከምንም ነው ። ውሃ በምድር ለሚኖሩ ፍጥረታት ሕይወታቸው ነው ። ከእሳት በቀር በሁሉም ፍጥረታት ውስጥ አለ ። ውሃ በዓይን ይታያል ፣ በእጅ ይዳሰሳ ል ፣ ግን አይጨበጥም ። በባህርዩ ከመሬት ረቂቅ ነው ። በውስጡ ሶስት ባህርያት ፡ ቅዝቃዜ ፣ እርጥበት ፣ ብርሃን ፤ ናቸው
4 እሳት ከአራቱ ባህርያት አንዱ ሲሆን የተፈጠረው ከምንም ነው ። በዓይን ይታያል ግን በእጅ አይጨበጥም አይዳሰስም ከመሬትና ከውሃ ይረቃል ። የእሳት ሶስት ባህርያት ፤ ብርሃን ሙቀት (ዋዕይ) ደረቅነት (ይብሰት) ናቸው ።
5 ነፋስ (አየር) ከአራቱ ባህርያት የመጨረሻ የሆነው ነፋስ በባህርዩ ከመሬት ከውሃና ከእሳት ይረቃል ። እንቅስቃሴው ይሰ ማል ። ነገር ግን በዓይን አይታይም ። በእጅ አይዳሰስም ። ዮሐ 3 ፡ 8 ። የነፋስ (አየር) 3 ባህርያት እርጥበት (ርጡብነት) ፣ ረቂቅነት ፣ ጸሊምነት (ጥቁርነት) ናቸው ።
ጥቁርነት የነፋስ ባህርይ ነው መባሉ ፤ በዓይን ታይቶ ሳይሆን ፤ ከጨለማ ባህርይ ጋር በመስማማቱና ተለይቶ ባለመታወቁ ነው ። እስመ ነፋስ ጸሊም በአርአያሁ እንዲል ። ነፋስ የተፈጠረው ከምንም ነው ።
የአራቱ ባህርያት የየራሳቸው ዋና ባህርይ መሬት ደረቅነት ፣ ውሃ ቀዝቃዛ ነት ፣ እሳት ብሩህነት ፣ ነፋስ ረቂቅነት ፣ ነው ።
አራቱ ባህርያት ለፍጥረታት ሁሉ መሠረት ናቸው ። እግዚአብሔር በምድር ያሉ ፍጥረታትን የፈጠራቸው ከአራቱ ባህርያት ሲሆን ፤ እነሱን ግን ያስገኛቸው ከምንም (ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ) ነው ።
ዓለመ ሰማይ
ሰባቱ ሰማያት ፤ እግዚአብሔር ሰማያትን ከእሳት ዋዕዩን (የማቃጠል ባህርዩን) ትቶ ብርሃኑን ብቻ በመውሰድ ፈጠራቸው ስማ ቸውም ከላይ ወደ ታች በሚከተለው መልኩ ይገለጻል ።
ጽርሐ አርያም 3. መንበረ መንግሥት 5. ራማ2. ሰማይ ውዱድ 4. ኢየሩሳሌም ሰማዊት 6. ኢዮር 7. ኤረር ናቸው ።
ጽርሐ አርያምለሰባቱም ሰማያት የመጨረሻ ክፍል ሲሆን ፤ ከላይ ወደታች ሲቆጠር የመጀመሪያ ደረጃያለው ነው ።
መንበረ መንግሥትእግዚአብሔር በወደደው መጠን ለወዳጆቹ የሚገለጥበት ፤ የክብሩ ዙፋን የተዘረጋበት ፤ ቅዱሳን መላ እክት በፊቱ እየሰገዱ ምስጋና የሚያቀርቡበት ፤ የሞቱ ሰዎች ነፍሳቸው ሰግዳ ፍርድ የምትቀበልበት ነው ። ኢሳ 6 ፥ 1 ። ሕዝቅ 1 ፥ 22 – 27 ። ራዕ 4 ፥ 2 ።
ሰማይ ውዱድበአራቱ መዐዝን ቁመው ዙፋኑን የተሸከሙ አርባዕቱ እንስሳ (የሰው ፤ የላም ፤ የንሥር ፤ የአንበሳ) ምስል ያላቸውና ዘወትር ዙፋኑን የሚያጥኑ ፳፬ ካህናተ ሰማይ ያሉበት የሰማይ ክፍል ነው ። ሕዝቅ 1 ፡ 4 – 75 ። ራዕ 4 ፥ 4
ኢየሩሳሌም ሰማያዊት (መንግስተ ሰማያት) በመጀመሪያ ሳጥናኤል (የዛሬው ዲያብሎስ) የነበረባት ፤ ጻድቃን ከምጽአት በኋላ የሚወርሷት ርስታቸው ናት ። ገላ 4 ፥ 26 ። ዕብ 12 ፥ 22 ። ዮሐ 14 ፥ 2 ።
ኢዮር ፤ 6 ራማ ፤ 7 ኤረር፤ሦሥቱም የመላእክት ዓለማት (መኖሪያዎች) ሲሆኑ ፤ ከዳግም ምጽዓት በኋላ ወዳለመኖር ሲያልፉ ቅዱሳን መላእክት ከጻድቃን ጋር በመንግስተ ሰማያት ይጠቃለላሉ (ይኖራሉ) ። ማቴ 22 ፥ 30 ። ከሰባቱ ሰማያት ቀጥሎ ያለውና ምጽንዓት የሚባለው የሰባቱ ሰማያት መሠረት ነው ።